بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በኾነው፡፡
تَبَّتْ يَدَآ أَبِى لَهَبٍۢ وَتَبَّ
የአቡ ለሀብ ሁለት እጆች ከሰሩ (ጠፉ፤ እርሱ) ከሰረም፡፡
مَآ أَغْنَىٰ عَنْهُ مَالُهُۥ وَمَا كَسَبَ
ከእርሱ ገንዘቡና ያም ያፈራው ሁሉ ምንም አልጠቀመውም፡፡
سَيَصْلَىٰ نَارًۭا ذَاتَ لَهَبٍۢ
የመንቀልቀል ባለቤት የኾነችን እሳት በእርግጥ ይገባል፡፡
وَٱمْرَأَتُهُۥ حَمَّالَةَ ٱلْحَطَبِ
ሚስቱም (ትገባለች)፤ እንጨት ተሸካሚ ስትኾን፡፡
فِى جِيدِهَا حَبْلٌۭ مِّن مَّسَدٍۭ
በአንገትዋ ላይ ከጭረት የኾነ ገመድ ያለባት ስትኾን፡፡