Surah 78: An-Naba — النبأ
عَمَّ يَتَسَآءَلُونَ
ከምን ነገር ይጠያየቃሉ?
عَنِ ٱلنَّبَإِ ٱلْعَظِيمِ
ከታላቁ ዜና (ከቁርኣን ይጠያየቃሉ)፡፡
ٱلَّذِى هُمْ فِيهِ مُخْتَلِفُونَ
ከዚያ እነርሱ በእርሱ የተለያዩበት ከኾነው፡፡
كَلَّا سَيَعْلَمُونَ
ይከልከሉ፤ ወደፊት (የሚደርስበቸውን) በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
ثُمَّ كَلَّا سَيَعْلَمُونَ
ከዚያም ይከልከሉ፤ ወደፊት ያውቃሉ፡፡
أَلَمْ نَجْعَلِ ٱلْأَرْضَ مِهَٰدًۭا
ምድርን ምንጣፍ አላደረግንምን?
وَٱلْجِبَالَ أَوْتَادًۭا
ጋራዎችንም ችካሎች አላደረግንምን?
وَخَلَقْنَٰكُمْ أَزْوَٰجًۭا
ብዙ ዓይነቶችም አድርገን ፈጠርናችሁ፡፡
وَجَعَلْنَا نَوْمَكُمْ سُبَاتًۭا
እንቅልፋችሁንም ዕረፍት አደረግን፡፡
وَجَعَلْنَا ٱلَّيْلَ لِبَاسًۭا
ሌሊቱንም ልባስ አደረግን፡፡
وَجَعَلْنَا ٱلنَّهَارَ مَعَاشًۭا
ቀኑንም (ለኑሮ) መስሪያ አደረግን፡፡
وَبَنَيْنَا فَوْقَكُمْ سَبْعًۭا شِدَادًۭا
ከበላያችሁም ሰባትን ብርቱዎች (ሰማያት) ገነባን፡፡
وَجَعَلْنَا سِرَاجًۭا وَهَّاجًۭا
አንጸባራቂ ብርሃንንም አደረግን፡፡
وَأَنزَلْنَا مِنَ ٱلْمُعْصِرَٰتِ مَآءًۭ ثَجَّاجًۭا
ከአረገዙት ደመናዎችም ተንቧቢ ውሃን አወረድን፡፡
لِّنُخْرِجَ بِهِۦ حَبًّۭا وَنَبَاتًۭا
በእርሱ እኽልንና ቅጠላ ቅጠልን እናወጣ ዘንድ (አወረድን)፡፡
وَجَنَّٰتٍ أَلْفَافًا
የተቆላለፉ አትክልቶችንም፡፡
إِنَّ يَوْمَ ٱلْفَصْلِ كَانَ مِيقَٰتًۭا
የመለያው ቀን የተወሰነ ጊዜ ነው፡፡
يَوْمَ يُنفَخُ فِى ٱلصُّورِ فَتَأْتُونَ أَفْوَاجًۭا
በቀንዱ በሚነፋና የተለያዩ ጭፍሮች ኾናችሁ በምትመጡ ቀን ነው፡፡
وَفُتِحَتِ ٱلسَّمَآءُ فَكَانَتْ أَبْوَٰبًۭا
ሰማይም በምትከፈትና (ባለ) ደጃፎችም በምትኾንበት፡፡
وَسُيِّرَتِ ٱلْجِبَالُ فَكَانَتْ سَرَابًا
ጋራዎችም በሚነዱበት (እንደ) ሲሪብዱም በሚኾኑበት (ቀን) ነው፡፡
إِنَّ جَهَنَّمَ كَانَتْ مِرْصَادًۭا
ገሀነም መጠባበቂያ (ስፍራ) ናት፡፡
لِّلطَّٰغِينَ مَـَٔابًۭا
ለሕግ ተላላፊዎች መመለሻ ስትኾን፡፡
لَّٰبِثِينَ فِيهَآ أَحْقَابًۭا
በውስጧ ብዙን ዘመናት ነዋሪዎች ሲኾኑ፤
لَّا يَذُوقُونَ فِيهَا بَرْدًۭا وَلَا شَرَابًا
በውስጧ ቅዝቃዜንም መጠጥንም አይቀምሱም፡፡
إِلَّا حَمِيمًۭا وَغَسَّاقًۭا
ግን ሙቅ ውሃንና እዥን (ይቀምሳሉ)፡፡
جَزَآءًۭ وِفَاقًا
ተስማሚን ምንዳ ይምመነዳሉ፡፡
إِنَّهُمْ كَانُوا۟ لَا يَرْجُونَ حِسَابًۭا
እነርሱ ምርመራን የማይፈሩ ነበሩና፡፡
وَكَذَّبُوا۟ بِـَٔايَٰتِنَا كِذَّابًۭا
በአንቀጾቻችንም ማስተባበልን አስተባበሉና፡፡
وَكُلَّ شَىْءٍ أَحْصَيْنَٰهُ كِتَٰبًۭا
ነገሩንም ሁሉ የተጻፈ ሲኾን አጠቃለልነው፡፡
فَذُوقُوا۟ فَلَن نَّزِيدَكُمْ إِلَّا عَذَابًا
ቅመሱም ቅጣትንም እንጅ (ሌላን) አንጨምራችሁም (ይባላሉ)፡፡
إِنَّ لِلْمُتَّقِينَ مَفَازًا
ለጥንቁቆቹ መዳኛ ስፍራ አልላቸው፡፡
حَدَآئِقَ وَأَعْنَٰبًۭا
አትክልቶችና ወይኖችም፡፡
وَكَوَاعِبَ أَتْرَابًۭا
እኩያዎች የኾኑ ጡተ ጉቻማዎችም፡፡
وَكَأْسًۭا دِهَاقًۭا
የተሞሉ ብርጭቆዎችም፡፡
لَّا يَسْمَعُونَ فِيهَا لَغْوًۭا وَلَا كِذَّٰبًۭا
በውስጧ ትርፍ ቃልንም ማስዋሸትንም አይሰሙም፡፡
جَزَآءًۭ مِّن رَّبِّكَ عَطَآءً حِسَابًۭا
ከጌታህ የኾነን ምንዳ በቂ ስጦታን (ተሰጡ)፡፡
رَّبِّ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلْأَرْضِ وَمَا بَيْنَهُمَا ٱلرَّحْمَٰنِ ۖ لَا يَمْلِكُونَ مِنْهُ خِطَابًۭا
የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ በጣም አዛኝ ከኾነው (ተመነዱ)፡፡ ከእርሱ ጋር መነጋገርን አይችሉም፡፡
يَوْمَ يَقُومُ ٱلرُّوحُ وَٱلْمَلَٰٓئِكَةُ صَفًّۭا ۖ لَّا يَتَكَلَّمُونَ إِلَّا مَنْ أَذِنَ لَهُ ٱلرَّحْمَٰنُ وَقَالَ صَوَابًۭا
መንፈሱ (ጂብሪል) መላእክቶቹም የተሰለፉ ኾነው በሚቆሙ ቀን አል-ረሕማን ለእርሱ የፈቀደለትና ትክክለኛን ቃል ያለ ሰው ቢኾን እንጅ (መነጋገርን አይችሉም)፡፡
ذَٰلِكَ ٱلْيَوْمُ ٱلْحَقُّ ۖ فَمَن شَآءَ ٱتَّخَذَ إِلَىٰ رَبِّهِۦ مَـَٔابًا
ይህ የተረጋገጠው ቀን ነው፡፡ የሻም ሰው ወደ ጌታው መመለስን ይይዛል፡፡
إِنَّآ أَنذَرْنَٰكُمْ عَذَابًۭا قَرِيبًۭا يَوْمَ يَنظُرُ ٱلْمَرْءُ مَا قَدَّمَتْ يَدَاهُ وَيَقُولُ ٱلْكَافِرُ يَٰلَيْتَنِى كُنتُ تُرَٰبًۢا
እኛ ሰው ሁሉ እጆቹ ያስቀደሙትን በሚያይበትና ከሓዲውም ዋ ምኞቴ! ምንነው ዐፈር በኾንኩ በሚልበት ቀን ቅርብ የኾነን ቅጣት አስጠነቀቅናችሁ፡፡
Surah 79: An-Naziat — النازعات
وَٱلنَّٰزِعَٰتِ غَرْقًۭا
በኃይል አውጪዎች በኾኑት፤
وَٱلنَّٰشِطَٰتِ نَشْطًۭا
በቀስታ መምዘዝንም መዘዦች በኾኑት፤
وَٱلسَّٰبِحَٰتِ سَبْحًۭا
መዋኘትም ዋኚዎች በኾኑት፤
فَٱلسَّٰبِقَٰتِ سَبْقًۭا
መቅደምንም ቀዳሚዎች በኾኑት፤
فَٱلْمُدَبِّرَٰتِ أَمْرًۭا
ነገርንም አስተናባሪዎች በኾኑት (መላእክት) እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
يَوْمَ تَرْجُفُ ٱلرَّاجِفَةُ
ተርገፍጋፊይቱ (ምድር) በምትርገፈገፍበት ቀን፤
تَتْبَعُهَا ٱلرَّادِفَةُ
ለጣቂይቱ የምትከተላት ስትኾን (ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
قُلُوبٌۭ يَوْمَئِذٍۢ وَاجِفَةٌ
በዚያ ቀን ልቦች ተሸባሪዎች ናቸው፡፡
أَبْصَٰرُهَا خَٰشِعَةٌۭ
ዓይኖቻቸው ተዋራጆች (አቀርቃሪዎች) ናቸው፡፡
يَقُولُونَ أَءِنَّا لَمَرْدُودُونَ فِى ٱلْحَافِرَةِ
«እኛ ወደ መጀመሪያይቱ ኹነታ ተመላሾች ነን?» ይላሉ፡፡
أَءِذَا كُنَّا عِظَٰمًۭا نَّخِرَةًۭ
«የበሰበሱ አጥንቶች በኾን ጊዜ (እንቀሰቀሳለን?)»
قَالُوا۟ تِلْكَ إِذًۭا كَرَّةٌ خَاسِرَةٌۭ
«ይህቺ ያን ጊዜ ባለ ከሳራ መመለስ ናት» ይላሉ፡፡
فَإِنَّمَا هِىَ زَجْرَةٌۭ وَٰحِدَةٌۭ
እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡
فَإِذَا هُم بِٱلسَّاهِرَةِ
ወዲያውኑም እነርሱ እንቅልፍ በሌለባት (ምድር) ላይ ይኾናሉ፡፡
هَلْ أَتَىٰكَ حَدِيثُ مُوسَىٰٓ
የሙሳ ወሬ መጣልህን?
إِذْ نَادَىٰهُ رَبُّهُۥ بِٱلْوَادِ ٱلْمُقَدَّسِ طُوًى
ጌታው በተቀደሰው ሸለቆ በጡዋ በጠራው ጊዜ፤
ٱذْهَبْ إِلَىٰ فِرْعَوْنَ إِنَّهُۥ طَغَىٰ
ወደ ፈርዖን ኺድ፡፡ እርሱ ወሰን አልፏልና፡፡
فَقُلْ هَل لَّكَ إِلَىٰٓ أَن تَزَكَّىٰ
በለውም፡- «ወደ መጥራራትህ ላንተ (መንገድ) አለህን?»
وَأَهْدِيَكَ إِلَىٰ رَبِّكَ فَتَخْشَىٰ
«ወደ ጌታህም ልመራህ ትፈራውም ዘንድ፤ (መንገድ አለህን?)» አለው፡፡
فَأَرَىٰهُ ٱلْءَايَةَ ٱلْكُبْرَىٰ
ታላቂቱንም ተዓምር አሳየው፡፡
فَكَذَّبَ وَعَصَىٰ
አስተባበለም፤ አመጸም፡፡
ثُمَّ أَدْبَرَ يَسْعَىٰ
ከዚያም (ለማጥፋት) የሚተጋ ኾኖ ዞረ፡፡
فَحَشَرَ فَنَادَىٰ
(ሰራዊቶቹን) ሰበሰበም፤ ተጣራም፡፡
فَقَالَ أَنَا۠ رَبُّكُمُ ٱلْأَعْلَىٰ
አለም፡- «እኔ ታላቁ ጌታችሁ ነኝ፡፡»
فَأَخَذَهُ ٱللَّهُ نَكَالَ ٱلْءَاخِرَةِ وَٱلْأُولَىٰٓ
አላህም በኋለኛይቱና በፊተኛይቱ (ቃል) ቅጣት ያዘው፡፡
إِنَّ فِى ذَٰلِكَ لَعِبْرَةًۭ لِّمَن يَخْشَىٰٓ
በዚህ ውስጥ ለሚፈራ ሰው በእርግጥ መገምገሚያ አለበት፡፡
ءَأَنتُمْ أَشَدُّ خَلْقًا أَمِ ٱلسَّمَآءُ ۚ بَنَىٰهَا
ባፈጣጠር እናንተ ይበልጥ የበረታችሁ ናችሁን? ወይንስ ሰማይ? (አላህ) ገነባት፡፡
رَفَعَ سَمْكَهَا فَسَوَّىٰهَا
ከፍታዋን አጓነ፤ አስተካከላትም፡፡
وَأَغْطَشَ لَيْلَهَا وَأَخْرَجَ ضُحَىٰهَا
ሌሊቷንም አጨለመ፡፡ ቀንዋንም ገለጸ፡፡
وَٱلْأَرْضَ بَعْدَ ذَٰلِكَ دَحَىٰهَآ
ምድርንም ከዚህ በኋላ ዘረጋት፡፡
أَخْرَجَ مِنْهَا مَآءَهَا وَمَرْعَىٰهَا
ውሃዋንና ግጦሿን ከእርሷ አወጣ፡፡
وَٱلْجِبَالَ أَرْسَىٰهَا
ጋራዎችንም አደላደላቸው፡፡
مَتَٰعًۭا لَّكُمْ وَلِأَنْعَٰمِكُمْ
ለእናንተና ለእንስሶቻችሁ መጣቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን አደረገ)፡፡
فَإِذَا جَآءَتِ ٱلطَّآمَّةُ ٱلْكُبْرَىٰ
ታላቂቱም መዐት በመጣች ጊዜ፣
يَوْمَ يَتَذَكَّرُ ٱلْإِنسَٰنُ مَا سَعَىٰ
ሰው ሁሉ የሠራውን በሚያስታውስበት ቀን፣
وَبُرِّزَتِ ٱلْجَحِيمُ لِمَن يَرَىٰ
ገሀነምም ለሚያይ ሰው በተገለጠች ጊዜ፣
فَأَمَّا مَن طَغَىٰ
የካደ ሰውማ፣
وَءَاثَرَ ٱلْحَيَوٰةَ ٱلدُّنْيَا
ቅርቢቱንም ሕይወት የመረጠ፣
فَإِنَّ ٱلْجَحِيمَ هِىَ ٱلْمَأْوَىٰ
ገሀነም እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡
وَأَمَّا مَنْ خَافَ مَقَامَ رَبِّهِۦ وَنَهَى ٱلنَّفْسَ عَنِ ٱلْهَوَىٰ
በጌታው ፊት መቆምን የፈራ ሰውማ ነፍሱንም ከዝንባሌዋ የከለከለ
فَإِنَّ ٱلْجَنَّةَ هِىَ ٱلْمَأْوَىٰ
ገነት እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡
يَسْـَٔلُونَكَ عَنِ ٱلسَّاعَةِ أَيَّانَ مُرْسَىٰهَا
«ከሰዓቲቱ መቼ ነው መኾኛዋ?» ሲሉ ይጠይቁሃል፡፡
فِيمَ أَنتَ مِن ذِكْرَىٰهَآ
አንተ እርሷን ከማስታወስ በምን ውስጥ ነህ?
إِلَىٰ رَبِّكَ مُنتَهَىٰهَآ
(የዕውቀት) መጨረሻዋ ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
إِنَّمَآ أَنتَ مُنذِرُ مَن يَخْشَىٰهَا
አንተ የሚፈራትን ሰው አስፈራሪ ብቻ ነህ፡፡
كَأَنَّهُمْ يَوْمَ يَرَوْنَهَا لَمْ يَلْبَثُوٓا۟ إِلَّا عَشِيَّةً أَوْ ضُحَىٰهَا
እነርሱ በሚያዩዋት ቀን ያንዲት ቀን ምሽትን ወይም ረፏዷን እንጅ ያልቆዩ ይመስላሉ፡፡
Surah 80: Abasa — عبس
عَبَسَ وَتَوَلَّىٰٓ
ፊቱን አጨፈገገ፤ ዞረም፡፡
أَن جَآءَهُ ٱلْأَعْمَىٰ
ዕውሩ ስለ መጣው፡፡
وَمَا يُدْرِيكَ لَعَلَّهُۥ يَزَّكَّىٰٓ
ምን ያሳውቅሃል? (ከኀጢአቶቹ) ሊጥራራ ይከጀላል፡፡
أَوْ يَذَّكَّرُ فَتَنفَعَهُ ٱلذِّكْرَىٰٓ
ወይም ሊገሠጽ ግሠጼይቱም ልትጠቅመው (ይከጀላል)፡፡
أَمَّا مَنِ ٱسْتَغْنَىٰ
የተብቃቃው ሰውማ፤
فَأَنتَ لَهُۥ تَصَدَّىٰ
አንተ ለእርሱ (ለእምነቱ በመጓጓት) በፈገግታ ትቀበለዋለህ፡፡
وَمَا عَلَيْكَ أَلَّا يَزَّكَّىٰ
ባይጥራራ (ባያምን) ባንተ ላይ ምንም የሌለብህ ስትኾን፡፡
وَأَمَّا مَن جَآءَكَ يَسْعَىٰ
እየገሰገሰ የመጣህ ሰውማ፤
وَهُوَ يَخْشَىٰ
እርሱ (አላህን) የሚፈራ ሲኾን፤
فَأَنتَ عَنْهُ تَلَهَّىٰ
አንተ ከእርሱ ትዝዘናጋለህ፡፡
كَلَّآ إِنَّهَا تَذْكِرَةٌۭ
ተከልከል፡፡ እርሷ ማስገንዘቢያ ናት፡፡
فَمَن شَآءَ ذَكَرَهُۥ
የሻም ሰው (ቁርኣኑን) ያስታውሰዋል፡፡
فِى صُحُفٍۢ مُّكَرَّمَةٍۢ
በተከበሩ ጽሑፎች ውስጥ ነው፡፡
مَّرْفُوعَةٍۢ مُّطَهَّرَةٍۭ
ከፍ በተደረገች ንጹሕ በተደረገች (ጽሑፍ ውስጥ ነው)፡፡
بِأَيْدِى سَفَرَةٍۢ
በጸሐፊዎቹ (መላእክት) እጆች (ንጹሕ የተደረገች)፡፡
كِرَامٍۭ بَرَرَةٍۢ
የተከበሩና ታዛዦች በኾኑት (ጸሐፊዎች እጆች)፡፡
قُتِلَ ٱلْإِنسَٰنُ مَآ أَكْفَرَهُۥ
ሰው ተረገመ፤ ምን ከሓዲ አደረገው?
مِنْ أَىِّ شَىْءٍ خَلَقَهُۥ
(ጌታው) በምን ነገር ፈጠረው? (አያስብምን?)
مِن نُّطْفَةٍ خَلَقَهُۥ فَقَدَّرَهُۥ
ከፍትወት ጠብታ ፈጠረው፤ መጠነውም፡፡
ثُمَّ ٱلسَّبِيلَ يَسَّرَهُۥ
ከዚያም (መውጫ) መንገዱን አገራው፡፡
ثُمَّ أَمَاتَهُۥ فَأَقْبَرَهُۥ
ከዚያም ገደለው፤ እንዲቀበርም አደረገው፡፡
ثُمَّ إِذَا شَآءَ أَنشَرَهُۥ
ከዚያም (ማንሳቱን) በሻ ጊዜ ያስነሳዋል፡፡
كَلَّا لَمَّا يَقْضِ مَآ أَمَرَهُۥ
በእውነት ያንን (ጌታው) ያዘዘውን ገና አልፈጸመም፡፡
فَلْيَنظُرِ ٱلْإِنسَٰنُ إِلَىٰ طَعَامِهِۦٓ
ሰውም ወደ ምግቡ ይመልከት፡፡
أَنَّا صَبَبْنَا ٱلْمَآءَ صَبًّۭا
እኛ ውሃን ማንቧቧትን ያንቧቧን መኾናችንን፡፡
ثُمَّ شَقَقْنَا ٱلْأَرْضَ شَقًّۭا
ከዚያም ምድርን (በደካማ ቡቃያ) መሰንጠቅን የሰነጠቅን፤
فَأَنۢبَتْنَا فِيهَا حَبًّۭا
በውስጧም እኽልን ያበቀልን፤
وَعِنَبًۭا وَقَضْبًۭا
ወይንንም፤ እርጥብ ያበቀልን፤
وَزَيْتُونًۭا وَنَخْلًۭا
የዘይት ወይራንም ዘንባባንም፤
وَحَدَآئِقَ غُلْبًۭا
ጭፍቆች አትክልቶችንም፤
وَفَٰكِهَةًۭ وَأَبًّۭا
ፍራፍሬንም ገለባንም፤ (ያበቀልን መኾናችንን ይመልከት)፡፡
مَّتَٰعًۭا لَّكُمْ وَلِأَنْعَٰمِكُمْ
ለእናንተም ለእንስሶቻችሁም መጠቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን ሠራን)፡፡
فَإِذَا جَآءَتِ ٱلصَّآخَّةُ
አደንቋሪይቱም (መከራ) በመጣች ጊዜ፤
يَوْمَ يَفِرُّ ٱلْمَرْءُ مِنْ أَخِيهِ
ሰው ከወንድሙ በሚሸሽበት ቀን፤
وَأُمِّهِۦ وَأَبِيهِ
ከናቱም ካባቱም፤
وَصَٰحِبَتِهِۦ وَبَنِيهِ
ከሚስቱም ከልጁም፤
لِكُلِّ ٱمْرِئٍۢ مِّنْهُمْ يَوْمَئِذٍۢ شَأْنٌۭ يُغْنِيهِ
ከእነርሱ ለየሰው ሁሉ በዚያ ቀን (ከሌላው) የሚያብቃቃው ኹነታ አልለው፡፡
وُجُوهٌۭ يَوْمَئِذٍۢ مُّسْفِرَةٌۭ
ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፤
ضَاحِكَةٌۭ مُّسْتَبْشِرَةٌۭ
ሳቂዎችም ተደሳቾችም ናቸው፡፡
وَوُجُوهٌۭ يَوْمَئِذٍ عَلَيْهَا غَبَرَةٌۭ
ፊቶችም በዚያ ቀን በላያቸው ላይ ትቢያ አልለባቸው፤
تَرْهَقُهَا قَتَرَةٌ
ጥቁረት ትሸፍናቸዋለች፤
أُو۟لَٰٓئِكَ هُمُ ٱلْكَفَرَةُ ٱلْفَجَرَةُ
እነዚያ እነሱ ከሓዲዎቹ አመጸኞቹ ናቸው፡፡
Surah 81: At-Takwir — التكوير
إِذَا ٱلشَّمْسُ كُوِّرَتْ
ፀሐይ በተጠቀለለች ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلنُّجُومُ ٱنكَدَرَتْ
ከዋክብትም በረገፉ ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلْجِبَالُ سُيِّرَتْ
ተራራዎችም በተነዱ ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلْعِشَارُ عُطِّلَتْ
የዐሥር ወር እርጉዞች ግመሎችም (ያለጠባቂ) በተተዉ ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلْوُحُوشُ حُشِرَتْ
እንስሳትም ሁሉ በተሰበሰቡ ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلْبِحَارُ سُجِّرَتْ
ባሕሮችም በተቃጠሉ ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلنُّفُوسُ زُوِّجَتْ
ነፍሶችም (በየአካሎቻቸው) በተቆራኙ ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلْمَوْءُۥدَةُ سُئِلَتْ
በሕይወቷ የተቀበረችውም ሴት ልጅ በተጠየቀች ጊዜ፤
بِأَىِّ ذَنۢبٍۢ قُتِلَتْ
በምን ወንጀል እንደ ተገደለች፤
وَإِذَا ٱلصُّحُفُ نُشِرَتْ
ጽሑፎችም በተዘረጉ ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلسَّمَآءُ كُشِطَتْ
ሰማይም በተገሸለጠች ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلْجَحِيمُ سُعِّرَتْ
ገሀነምም በተነደደች ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلْجَنَّةُ أُزْلِفَتْ
ገነትም በተቀረበች ጊዜ፤
عَلِمَتْ نَفْسٌۭ مَّآ أَحْضَرَتْ
ነፍስ ሁሉ (ከሥራ) ያቀረበችውን ታውቃለች፤
فَلَآ أُقْسِمُ بِٱلْخُنَّسِ
ተመላሾችም በኾኑት (ዐዋድያት) እምላለሁ፡፡
ٱلْجَوَارِ ٱلْكُنَّسِ
ኺያጆች ገቢዎች በኾኑት (ከዋክብት)፡፡
وَٱلَّيْلِ إِذَا عَسْعَسَ
በሌሊቱም (ጨለማውን) በጠነሰሰ ጊዜ፤
وَٱلصُّبْحِ إِذَا تَنَفَّسَ
በንጋቱም (በብርሃን) በተነፈሰ ጊዜ፤ (እምላለሁ)፡፡
إِنَّهُۥ لَقَوْلُ رَسُولٍۢ كَرِيمٍۢ
እርሱ (ቁርኣን) የክቡር መልክተኛ ቃል ነው፡፡
ذِى قُوَّةٍ عِندَ ذِى ٱلْعَرْشِ مَكِينٍۢ
የኀይል ባለቤት በዙፋኑ ባለ ቤት ዘንድ ባለሟል የኾነ፡፡
مُّطَاعٍۢ ثَمَّ أَمِينٍۢ
በዚያ ስፍራ ትእዛዙ ተሰሚ፤ ታማኝ የኾነ (መልክተኛ ቃል) ነው፡፡
وَمَا صَاحِبُكُم بِمَجْنُونٍۢ
ነቢያችሁም በፍጹም ዕብድ አይደለም፡፡
وَلَقَدْ رَءَاهُ بِٱلْأُفُقِ ٱلْمُبِينِ
በግልጹ አድማስም በእርግጥ አይቶታል፡፡
وَمَا هُوَ عَلَى ٱلْغَيْبِ بِضَنِينٍۢ
እርሱም በሩቁ ወሬ ላይ ሰሳች (ንፉግ) አይደለም፡፡
وَمَا هُوَ بِقَوْلِ شَيْطَٰنٍۢ رَّجِيمٍۢ
እርሱም (ቁርኣን) የእርጉም ሰይጣን ቃል አይደለም፡፡
فَأَيْنَ تَذْهَبُونَ
ታዲያ ወዴት ትኼዳላችሁ?
إِنْ هُوَ إِلَّا ذِكْرٌۭ لِّلْعَٰلَمِينَ
እርሱ የዓለማት መገሠጫ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
لِمَن شَآءَ مِنكُمْ أَن يَسْتَقِيمَ
ከናንተ ቀጥተኛ መኾንን ለሻ ሰው (መገሰጫ ነው)፡፡
وَمَا تَشَآءُونَ إِلَّآ أَن يَشَآءَ ٱللَّهُ رَبُّ ٱلْعَٰلَمِينَ
የዓለማት ጌታ አላህ ካልሻም አትሹም፡፡
Surah 82: Al-Infitar — الإنفطار
إِذَا ٱلسَّمَآءُ ٱنفَطَرَتْ
ሰማይ በተሰነጠቀች ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلْكَوَاكِبُ ٱنتَثَرَتْ
ከዋክብትም ተበታትነው በወደቁ ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلْبِحَارُ فُجِّرَتْ
ባሕሮችም በተከፈቱና በተደበላለቁ ጊዜ፤
وَإِذَا ٱلْقُبُورُ بُعْثِرَتْ
መቃብሮችም በተገለባበጡና (ሙታን) በተነሱ ጊዜ፤
عَلِمَتْ نَفْسٌۭ مَّا قَدَّمَتْ وَأَخَّرَتْ
ማንኛይቱም ነፍስ ያስቀደመችውንና ያቆየችውን ታውቃለች፡፡
يَٰٓأَيُّهَا ٱلْإِنسَٰنُ مَا غَرَّكَ بِرَبِّكَ ٱلْكَرِيمِ
አንተ ሰው ሆይ! በቸሩ ጌታህ ምን አታለለህ?
ٱلَّذِى خَلَقَكَ فَسَوَّىٰكَ فَعَدَلَكَ
በዚያ በፈጠረህ አካለ ሙሉም ባደረገህ ባስተካከለህም፡፡
فِىٓ أَىِّ صُورَةٍۢ مَّا شَآءَ رَكَّبَكَ
በማንኛውም በሻው ቅርፅ በገጣጠመህ (ጌታህ ምን አታለለህ)፡፡
كَلَّا بَلْ تُكَذِّبُونَ بِٱلدِّينِ
ተከልከሉ፤ በእውነቱ በፍርዱ ቀን ታስተባብላላችሁ፡፡
وَإِنَّ عَلَيْكُمْ لَحَٰفِظِينَ
በእናንተ ላይ ተጠባባቂዎች ያሉባችሁ፤ ስትኾኑ፤
كِرَامًۭا كَٰتِبِينَ
የተከበሩ ጸሐፊዎች የኾኑ፤ (ተጠባባቂዎች)፡፡
يَعْلَمُونَ مَا تَفْعَلُونَ
የምትሠሩትን ሁሉ የሚያውቁ፡፡
إِنَّ ٱلْأَبْرَارَ لَفِى نَعِيمٍۢ
እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በገነት ውስጥ ናቸው፡፡
وَإِنَّ ٱلْفُجَّارَ لَفِى جَحِيمٍۢ
ከሓዲዎቹም በእርግጥ በገሀነም ውስጥ ናቸው፡፡
يَصْلَوْنَهَا يَوْمَ ٱلدِّينِ
በፍርዱ ቀን ይገቧታል፡፡
وَمَا هُمْ عَنْهَا بِغَآئِبِينَ
እነርሱም ከርሷ ራቂዎች አይደሉም፡፡
وَمَآ أَدْرَىٰكَ مَا يَوْمُ ٱلدِّينِ
የፍርድ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?
ثُمَّ مَآ أَدْرَىٰكَ مَا يَوْمُ ٱلدِّينِ
ከዚያም የፍርዱ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?
يَوْمَ لَا تَمْلِكُ نَفْسٌۭ لِّنَفْسٍۢ شَيْـًۭٔا ۖ وَٱلْأَمْرُ يَوْمَئِذٍۢ لِّلَّهِ
(እርሱ) ማንኛይቱም ነፍስ ለሌላይቱ ነፍስ ምንም ማድረግን የማትችልበት ቀን ነው፡፡ ነገሩም ሁሉ በዚያ ቀን ለአላህ ብቻ ነው፡፡
Surah 83: Al-Mutaffifin — المطففين
وَيْلٌۭ لِّلْمُطَفِّفِينَ
ለሰላቢዎች ወዮላቸው፡፡
ٱلَّذِينَ إِذَا ٱكْتَالُوا۟ عَلَى ٱلنَّاسِ يَسْتَوْفُونَ
ለእነዚያ ከሰዎች ባስሰፈሩ ጊዜ የሚያስሞሉ፡፡
وَإِذَا كَالُوهُمْ أَو وَّزَنُوهُمْ يُخْسِرُونَ
ለእነርሱም (ለሰዎቹ) በሰፈሩ ወይም በመዘኑላቸው ጊዜ የሚያጎድሉ (ለኾኑት)፡፡
أَلَا يَظُنُّ أُو۟لَٰٓئِكَ أَنَّهُم مَّبْعُوثُونَ
እነዚያ እነርሱ ተቀስቃሾች መኾናቸውን አያውቁምን?
لِيَوْمٍ عَظِيمٍۢ
በታላቁ ቀን፡፡
يَوْمَ يَقُومُ ٱلنَّاسُ لِرَبِّ ٱلْعَٰلَمِينَ
ሰዎች ሁሉ ለዓለማት ጌታ (ፍርድ)፤ በሚቆሙበት ቀን (ተቀስቃሾች መኾናቸውን)፡፡
كَلَّآ إِنَّ كِتَٰبَ ٱلْفُجَّارِ لَفِى سِجِّينٍۢ
በእውነት የከሓዲዎቹ (የሰላቢዎቹ) መጽሐፍ በእርግጥ በሲጂን ውስጥ ነው፡፡
وَمَآ أَدْرَىٰكَ مَا سِجِّينٌۭ
ሲጂንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?
كِتَٰبٌۭ مَّرْقُومٌۭ
የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡
وَيْلٌۭ يَوْمَئِذٍۢ لِّلْمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
ٱلَّذِينَ يُكَذِّبُونَ بِيَوْمِ ٱلدِّينِ
ለእነዚያ በፍርዱ ቀን ለሚያስተባብሉት፡፡
وَمَا يُكَذِّبُ بِهِۦٓ إِلَّا كُلُّ مُعْتَدٍ أَثِيمٍ
በእርሱም ወሰን አላፊ ኀጢአተኛ ሁሉ እንጅ ሌላ አያስተባብልም፡፡
إِذَا تُتْلَىٰ عَلَيْهِ ءَايَٰتُنَا قَالَ أَسَٰطِيرُ ٱلْأَوَّلِينَ
አንቀጾቻችን በእርሱ ላይ በተነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል፡፡
كَلَّا ۖ بَلْ ۜ رَانَ عَلَىٰ قُلُوبِهِم مَّا كَانُوا۟ يَكْسِبُونَ
ይከልከል፤ ይልቁንም በልቦቻቸው ላይ ይሠሩት የነበሩት (ኀጢአት) ደገደገባቸው፡፡
كَلَّآ إِنَّهُمْ عَن رَّبِّهِمْ يَوْمَئِذٍۢ لَّمَحْجُوبُونَ
ይከልከሉ፤ እነርሱ በዚያ ቀን ከጌታቸው (ማየት) ተጋራጆች ናቸው፡፡
ثُمَّ إِنَّهُمْ لَصَالُوا۟ ٱلْجَحِيمِ
ከዚያም እነርሱ በእርግጥ ገሀነምን ገቢዎች ናቸው፡፡
ثُمَّ يُقَالُ هَٰذَا ٱلَّذِى كُنتُم بِهِۦ تُكَذِّبُونَ
ከዚያም «ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉበት የነበራችሁት ነው» ይባላሉ፡፡
كَلَّآ إِنَّ كِتَٰبَ ٱلْأَبْرَارِ لَفِى عِلِّيِّينَ
በእውነቱ የእውነተኞቹ ምእምናን መጽሐፍ በዒሊዮን ውስጥ ነው፡፡
وَمَآ أَدْرَىٰكَ مَا عِلِّيُّونَ
ዒሊዮንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?
كِتَٰبٌۭ مَّرْقُومٌۭ
የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡
يَشْهَدُهُ ٱلْمُقَرَّبُونَ
ባለሟልዎቹ ይጣዱታል፡፡
إِنَّ ٱلْأَبْرَارَ لَفِى نَعِيمٍ
እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በድሎት (ገነት) ውስጥ ናቸው፡፡
عَلَى ٱلْأَرَآئِكِ يَنظُرُونَ
በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው ይመለከታሉ፡፡
تَعْرِفُ فِى وُجُوهِهِمْ نَضْرَةَ ٱلنَّعِيمِ
በፊቶቻቸው ላይ የድሎትን ውበት ታውቃለህ፡፡
يُسْقَوْنَ مِن رَّحِيقٍۢ مَّخْتُومٍ
ተጣርቶ ከታተመ ጠጅ ይጠጣሉ፡፡
خِتَٰمُهُۥ مِسْكٌۭ ۚ وَفِى ذَٰلِكَ فَلْيَتَنَافَسِ ٱلْمُتَنَٰفِسُونَ
ማተሚያው ምስክ ከኾነ፤ በዚህም ተሽቀዳዳሚዎች ይሽቀዳደሙ፡፡
وَمِزَاجُهُۥ مِن تَسْنِيمٍ
መበረዣውም ከተስኒም ነው፡፡
عَيْنًۭا يَشْرَبُ بِهَا ٱلْمُقَرَّبُونَ
ባለሟሎቹ ከእርሷ የሚጠጡላት ምንጭ ናት፡፡
إِنَّ ٱلَّذِينَ أَجْرَمُوا۟ كَانُوا۟ مِنَ ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ يَضْحَكُونَ
እነዚያ ያምመጹት በእነዚያ ባመኑት በእርግጥ ይስቁ ነበሩ፡፡
وَإِذَا مَرُّوا۟ بِهِمْ يَتَغَامَزُونَ
በእነርሱም ላይ ባለፉ ጊዜ ይጠቃቀሱ ነበር፡፡
وَإِذَا ٱنقَلَبُوٓا۟ إِلَىٰٓ أَهْلِهِمُ ٱنقَلَبُوا۟ فَكِهِينَ
ወደ ቤተሰቦቻቸውም በተመለሱ ጊዜ (በመሳለቃቸው) ተደሳቾች ኾነው ይመለሱ ነበር፡፡
وَإِذَا رَأَوْهُمْ قَالُوٓا۟ إِنَّ هَٰٓؤُلَآءِ لَضَآلُّونَ
ባዩዋቸውም ጊዜ «እነዚህ በእርግጥ ተሳሳቾች ናቸው» ይሉ ነበር፡፡
وَمَآ أُرْسِلُوا۟ عَلَيْهِمْ حَٰفِظِينَ
በነርሱ ላይ ተጠባባቂዎች ተደርገው ያልተላኩ ሲኾኑ፡፡
فَٱلْيَوْمَ ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ مِنَ ٱلْكُفَّارِ يَضْحَكُونَ
ዛሬ (በትንሣኤ ቀን) እነዚያ ያመኑት በከሓዲዎቹ ይስቃሉ፡፡
عَلَى ٱلْأَرَآئِكِ يَنظُرُونَ
በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው የሚመለከቱ ሲኾኑ (ይስቃሉ)፡፡
هَلْ ثُوِّبَ ٱلْكُفَّارُ مَا كَانُوا۟ يَفْعَلُونَ
ከሓዲዎች ይሠሩት የነበሩትን (ዋጋ) ተመነዱን? (ይላሉ)፡፡
Surah 84: Al-Inshiqaq — الإنشقاق
إِذَا ٱلسَّمَآءُ ٱنشَقَّتْ
ሰማይ በተቀደደች ጊዜ፤
وَأَذِنَتْ لِرَبِّهَا وَحُقَّتْ
ለጌታዋም (ትዕዛዝ) በሰማች ጊዜ፤ (ልትሰማ) ተገባትም፤
وَإِذَا ٱلْأَرْضُ مُدَّتْ
ምድርም በተለጠጠች ጊዜ፤
وَأَلْقَتْ مَا فِيهَا وَتَخَلَّتْ
በውስጧ ያለውንም ሁሉ በጣለችና ባዶ በኾነች ጊዜ፤
وَأَذِنَتْ لِرَبِّهَا وَحُقَّتْ
ለጌታዋም በሰማች ጊዜ፤ (መስማት) ተገባትም፤ (ሰው ሁሉ ሥራውን ይገናኛል)፡፡
يَٰٓأَيُّهَا ٱلْإِنسَٰنُ إِنَّكَ كَادِحٌ إِلَىٰ رَبِّكَ كَدْحًۭا فَمُلَٰقِيهِ
አንተ ሰው ሆይ! አንተ ጌታህን (በሞት) እስከምትገናኝ ድረስ ልፋትን ለፊ ነህ፤ ተገናኚውም ነህ፡፡
فَأَمَّا مَنْ أُوتِىَ كِتَٰبَهُۥ بِيَمِينِهِۦ
መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ፤
فَسَوْفَ يُحَاسَبُ حِسَابًۭا يَسِيرًۭا
በእርግጥ ቀላልን ምርመራ ይመረመራል፡፡
وَيَنقَلِبُ إِلَىٰٓ أَهْلِهِۦ مَسْرُورًۭا
ወደ ቤተሰቦቹም ተደሳች ኾኖ ይመለሳል፡፡
وَأَمَّا مَنْ أُوتِىَ كِتَٰبَهُۥ وَرَآءَ ظَهْرِهِۦ
መጽሐፉን በጀርባው ኋላ የተሰጠ ሰውማ፤
فَسَوْفَ يَدْعُوا۟ ثُبُورًۭا
(ዋ! ጥፋቴ በማለት) ጥፋትን በእርግጥ ይጠራል፡፡
وَيَصْلَىٰ سَعِيرًا
የተጋጋመች እሳትንም ይገባል፡፡
إِنَّهُۥ كَانَ فِىٓ أَهْلِهِۦ مَسْرُورًا
እርሱ በቤተሰቡ ውስጥ ተደሳች ነበርና፡፡
إِنَّهُۥ ظَنَّ أَن لَّن يَحُورَ
እርሱ (ወደ አላህ) የማይመለስ መኾኑን አስቧልና፡፡
بَلَىٰٓ إِنَّ رَبَّهُۥ كَانَ بِهِۦ بَصِيرًۭا
አይደለም (ይመለሳል)፡፡ ጌታው በእርሱ (መመለስ) ዐዋቂ ነበር፤ (ነውም)፡፡
فَلَآ أُقْسِمُ بِٱلشَّفَقِ
አትካዱ፤ በወጋገኑ እምላለሁ፡፡
وَٱلَّيْلِ وَمَا وَسَقَ
በሌሊቱም በሰበሰውም ሁሉ፤
وَٱلْقَمَرِ إِذَا ٱتَّسَقَ
በጨረቃውም በሞላ ጊዜ (እምላለሁ)፡፡
لَتَرْكَبُنَّ طَبَقًا عَن طَبَقٍۢ
ከኹነታ በኋላ ወደ ሌላ ኹነታ ትለዋወጣላችሁ፡፡
فَمَا لَهُمْ لَا يُؤْمِنُونَ
የማያምኑት ለእነርሱ ምን አላቸው?
وَإِذَا قُرِئَ عَلَيْهِمُ ٱلْقُرْءَانُ لَا يَسْجُدُونَ ۩
በእነርሱም ላይ ቁርኣን በተነበበ ጊዜ የማይሰግዱት፤ (ምንአላቸው?)
بَلِ ٱلَّذِينَ كَفَرُوا۟ يُكَذِّبُونَ
በእርግጡ እነዚያ የካዱት (በትንሣኤ) ያስተባብላሉ፡፡
وَٱللَّهُ أَعْلَمُ بِمَا يُوعُونَ
አላህም (በልቦቻቸው) የሚቆጥሩትን ዐዋቂ ነው፡፡
فَبَشِّرْهُم بِعَذَابٍ أَلِيمٍ
በአሳማሚ ቅጣትም አብስራቸው፡፡
إِلَّا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ وَعَمِلُوا۟ ٱلصَّٰلِحَٰتِ لَهُمْ أَجْرٌ غَيْرُ مَمْنُونٍۭ
ግን እነዚያ ያመኑና መልካሞችን የሠሩ ለእነርሱ የማይቆረጥ ምንዳ አልላቸው፡፡
Surah 85: Al-Buruj — البروج
وَٱلسَّمَآءِ ذَاتِ ٱلْبُرُوجِ
የቡርጆች ባለቤት በኾነችው ሰማይ እምላለሁ፡፡
وَٱلْيَوْمِ ٱلْمَوْعُودِ
በተቀጠረው ቀንም፤
وَشَاهِدٍۢ وَمَشْهُودٍۢ
በተጣጅና በሚጣዱትም፤ (እምላለሁ)፡፡
قُتِلَ أَصْحَٰبُ ٱلْأُخْدُودِ
የጉድቡ ባለቤቶች ተረገሙ፡፡
ٱلنَّارِ ذَاتِ ٱلْوَقُودِ
የማገዶ ባለቤት የኾነቺው እሳት (ባለቤቶች)፡፡
إِذْ هُمْ عَلَيْهَا قُعُودٌۭ
እነርሱ በርሷ (አፋፍ) ላይ ተቀማጮች በኾኑ ጊዜ፤ (ተረገሙ)፡፡
وَهُمْ عَلَىٰ مَا يَفْعَلُونَ بِٱلْمُؤْمِنِينَ شُهُودٌۭ
እነርሱም በምእምናኖቹ በሚሠሩት (ማሰቃየት) ላይ መስካሪዎች ናቸው፡፡
وَمَا نَقَمُوا۟ مِنْهُمْ إِلَّآ أَن يُؤْمِنُوا۟ بِٱللَّهِ ٱلْعَزِيزِ ٱلْحَمِيدِ
ከእነርሱም በአላህ አሸናፊው፣ ምስጉኑ በኾነው (ጌታ) ማመናቸውን እንጅ ሌላ ምንም አልጠሉም፡፡
ٱلَّذِى لَهُۥ مُلْكُ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلْأَرْضِ ۚ وَٱللَّهُ عَلَىٰ كُلِّ شَىْءٍۢ شَهِيدٌ
በእዚያ የሰማያትና የምድር ንግሥና ለእርሱ ብቻ በኾነው (አላህ ማመናቸውን)፡፡ አላህም በነገሩ ሁሉ ላይ መስካሪ ነው፡፡
إِنَّ ٱلَّذِينَ فَتَنُوا۟ ٱلْمُؤْمِنِينَ وَٱلْمُؤْمِنَٰتِ ثُمَّ لَمْ يَتُوبُوا۟ فَلَهُمْ عَذَابُ جَهَنَّمَ وَلَهُمْ عَذَابُ ٱلْحَرِيقِ
እነዚያ ምእምንንና ምእምናትን ያሰቃዩ፣ ከዚያም ያልተጸጸቱ ለእነርሱ የገሀነም ቅጣት አልላቸው፡፡ ለእነርሱም የመቃጠሉ ስቃይ አልላቸው፡፡
إِنَّ ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ وَعَمِلُوا۟ ٱلصَّٰلِحَٰتِ لَهُمْ جَنَّٰتٌۭ تَجْرِى مِن تَحْتِهَا ٱلْأَنْهَٰرُ ۚ ذَٰلِكَ ٱلْفَوْزُ ٱلْكَبِيرُ
እነዚያ ያመኑና መልካም ሥራዎችንም የሠሩ ለእነርሱ ከሥሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው ገነቶች አሏቸው፡፡ ይህ ታላቅ ማግኘት ነው፡፡
إِنَّ بَطْشَ رَبِّكَ لَشَدِيدٌ
የጌታህ በኀይል መያዝ ብርቱ ነው፡፡
إِنَّهُۥ هُوَ يُبْدِئُ وَيُعِيدُ
እነሆ እርሱ መፍጠርን ይጀምራል፤ ይመልሳልም፡፡
وَهُوَ ٱلْغَفُورُ ٱلْوَدُودُ
እርሱም ምሕረተ ብዙ ወዳድ ነው፡፡
ذُو ٱلْعَرْشِ ٱلْمَجِيدُ
የዙፋኑ ባለቤት የላቀው ነው፡፡
فَعَّالٌۭ لِّمَا يُرِيدُ
የሚሻውን ሁሉ ሠሪ ነው፡፡
هَلْ أَتَىٰكَ حَدِيثُ ٱلْجُنُودِ
የሰራዊቶቹ ወሬ መጣልህን?
فِرْعَوْنَ وَثَمُودَ
የፈርዖንና የሰሙድ፤ (ወሬ)፡፡
بَلِ ٱلَّذِينَ كَفَرُوا۟ فِى تَكْذِيبٍۢ
በእውነቱ እነዚያ የካዱት በማስተባበል ውስጥ ናቸው፡፡
وَٱللَّهُ مِن وَرَآئِهِم مُّحِيطٌۢ
አላህም በዙሪያቸው (በዕውቀቱ) ከባቢ ነው፡፡
بَلْ هُوَ قُرْءَانٌۭ مَّجِيدٌۭ
ይልቁንም እርሱ የከበረ ቁርኣን ነው፡፡
فِى لَوْحٍۢ مَّحْفُوظٍۭ
የተጠበቀ በኾነ ሰሌዳ ውስጥ ነው፡፡
Surah 86: At-Tariq — الطارق
وَٱلسَّمَآءِ وَٱلطَّارِقِ
በሰማዩ በሌሊት መጪውም እምላለሁ፡፡
وَمَآ أَدْرَىٰكَ مَا ٱلطَّارِقُ
የሌሊት መጪውም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?
ٱلنَّجْمُ ٱلثَّاقِبُ
ጨለማን ቀዳጁ ኮከብ ነው፡፡
إِن كُلُّ نَفْسٍۢ لَّمَّا عَلَيْهَا حَافِظٌۭ
ነፍስ ሁሉ በእርሷ ላይ ጠባቂ ያለባት እንጅ ሌላ አይደለችም፡፡
فَلْيَنظُرِ ٱلْإِنسَٰنُ مِمَّ خُلِقَ
ሰውም ከምን እንደተፈጠረ ይመልከት፡፡
خُلِقَ مِن مَّآءٍۢ دَافِقٍۢ
ከተስፈንጣሪ ውሃ ተፈጠረ፡፡
يَخْرُجُ مِنۢ بَيْنِ ٱلصُّلْبِ وَٱلتَّرَآئِبِ
ከጀርባና ከእርግብግብቶች መካከል የሚወጣ ከኾነ (ውሃ)፡፡
إِنَّهُۥ عَلَىٰ رَجْعِهِۦ لَقَادِرٌۭ
እርሱ (አላህ) በመመለሱ ላይ በእርግጥ ቻይ ነው፡፡
يَوْمَ تُبْلَى ٱلسَّرَآئِرُ
ምስጢሮች በሚገለጡበት ቀን፡፡
فَمَا لَهُۥ مِن قُوَّةٍۢ وَلَا نَاصِرٍۢ
ለእርሱም (ለሰው) ኀይልና ረዳት ምንም የለውም፡፡
وَٱلسَّمَآءِ ذَاتِ ٱلرَّجْعِ
የመመለስ ባለቤት በኾነችው ሰማይም እምላለሁ፡፡
وَٱلْأَرْضِ ذَاتِ ٱلصَّدْعِ
(በበቃይ) የመሰንጠቅ ባለቤት በኾነችው ምድርም፤
إِنَّهُۥ لَقَوْلٌۭ فَصْلٌۭ
እርሱ (እውነትን ከውሸት) የሚለይ ቃል ነው፡፡
وَمَا هُوَ بِٱلْهَزْلِ
እርሱም ቀልድ አይደለም፡፡
إِنَّهُمْ يَكِيدُونَ كَيْدًۭا
እነርሱ በእርግጥ ተንኮልን ይሠራሉ፡፡
وَأَكِيدُ كَيْدًۭا
(እኔ) ተንኮልንም እመልሳለሁ፡፡
فَمَهِّلِ ٱلْكَٰفِرِينَ أَمْهِلْهُمْ رُوَيْدًۢا
ከሓዲዎችንም ቀን ስጣቸው፡፡ ጥቂትን ጊዜ አቆያቸው፡፡
Surah 87: Al-Ala — الأعلى
سَبِّحِ ٱسْمَ رَبِّكَ ٱلْأَعْلَى
ከሁሉ በላይ የኾነውን ጌታህን ስም አሞግሥ፡፡
ٱلَّذِى خَلَقَ فَسَوَّىٰ
የዚያን (ሁሉን ነገር) የፈጠረውን ያስተካከለውንም፡፡
وَٱلَّذِى قَدَّرَ فَهَدَىٰ
የዚያንም የወሰነውን፡፡ (ለተፈጠረለት ነገር) የመራውንም፡፡
وَٱلَّذِىٓ أَخْرَجَ ٱلْمَرْعَىٰ
የዚያንም ግጦሽን (ለምለም አድርጎ) ያወጣውን፡፡
فَجَعَلَهُۥ غُثَآءً أَحْوَىٰ
(ከዚያ) ደረቅ ጥቁር ያደረገውንም (አምላክ ስም አሞግስ)፡፡
سَنُقْرِئُكَ فَلَا تَنسَىٰٓ
(ቁርኣንን) በእርግጥ እናስነብብሃለን፤ አትረሳምም፡፡
إِلَّا مَا شَآءَ ٱللَّهُ ۚ إِنَّهُۥ يَعْلَمُ ٱلْجَهْرَ وَمَا يَخْفَىٰ
አላህ ከሻው ነገር በስተቀር፡፡ እርሱ ግልጹን የሚሸሸገውንም ሁሉ ያውቃልና፡፡
وَنُيَسِّرُكَ لِلْيُسْرَىٰ
ለገሪቱም (ሕግጋት) እንገጥምሃለን፡፡
فَذَكِّرْ إِن نَّفَعَتِ ٱلذِّكْرَىٰ
ግሣጼይቱ ብትጠቅም (ሰዎችን) ገሥጽም፡፡
سَيَذَّكَّرُ مَن يَخْشَىٰ
(አላህን) የሚፈራ ሰው በእርግጥ ይገሠጻል፡፡
وَيَتَجَنَّبُهَا ٱلْأَشْقَى
መናጢውም ይርቃታል፡፡
ٱلَّذِى يَصْلَى ٱلنَّارَ ٱلْكُبْرَىٰ
ያ ታላቂቱን እሳት የሚገባው፡፡
ثُمَّ لَا يَمُوتُ فِيهَا وَلَا يَحْيَىٰ
ከዚያም በእርሷ ውስጥ አይሞትም ሕያውም አይኾንም፡፡
قَدْ أَفْلَحَ مَن تَزَكَّىٰ
የተጥራራ ሰው በእርግጥ ዳነ፡፡
وَذَكَرَ ٱسْمَ رَبِّهِۦ فَصَلَّىٰ
የጌታውንም ስም ያወሳና የሰገደ፡፡
بَلْ تُؤْثِرُونَ ٱلْحَيَوٰةَ ٱلدُّنْيَا
ይልቁንም ቅርቢቱን ሕይወት ትመርጣላችሁ፡፡
وَٱلْءَاخِرَةُ خَيْرٌۭ وَأَبْقَىٰٓ
መጨረሻይቱ (ሕይወት) በላጭ ሁል ጊዜ ዘውታሪም ስትኾን፡፡
إِنَّ هَٰذَا لَفِى ٱلصُّحُفِ ٱلْأُولَىٰ
ይህ በፊተኞቹ መጻሕፍት ውስጥ ያልለ ነው፡፡
صُحُفِ إِبْرَٰهِيمَ وَمُوسَىٰ
በኢብራሂምና በሙሳ ጽሑፎች ውስጥ፡፡
Surah 88: Al-Ghashiyah — الغاشية
هَلْ أَتَىٰكَ حَدِيثُ ٱلْغَٰشِيَةِ
የሸፋኝቱ (ትንሣኤ) ወሬ መጣህን?
وُجُوهٌۭ يَوْمَئِذٍ خَٰشِعَةٌ
ፊቶች በዚያ ቀን ተዋራጆች ናቸው፡፡
عَامِلَةٌۭ نَّاصِبَةٌۭ
ሠሪዎች ለፊዎች ናቸው፡፡
تَصْلَىٰ نَارًا حَامِيَةًۭ
ተኳሳን እሳት ይገባሉ፡፡
تُسْقَىٰ مِنْ عَيْنٍ ءَانِيَةٍۢ
በጣም ከፈላች ምንጭ ይጋታሉ፡፡
لَّيْسَ لَهُمْ طَعَامٌ إِلَّا مِن ضَرِيعٍۢ
ለእነርሱ ዶሪዕ ከሚባል (እሾሃም) ዛፍ እንጅ ሌላ ምግብ የላቸውም፡፡
لَّا يُسْمِنُ وَلَا يُغْنِى مِن جُوعٍۢ
የማያሰባ ከረኃብም የማያብቃቃ ከኾነው፡፡
وُجُوهٌۭ يَوْمَئِذٍۢ نَّاعِمَةٌۭ
ፊቶች በዚያ ቀን ተቀማጣዮች ናቸው፡፡
لِّسَعْيِهَا رَاضِيَةٌۭ
ለሥራቸው ተደሳቾች ናቸው፡፡
فِى جَنَّةٍ عَالِيَةٍۢ
በከፍተኛ ገነት ውስጥ ናቸው፡፡
لَّا تَسْمَعُ فِيهَا لَٰغِيَةًۭ
በውስጧ ውድቅን ነገር አይሰሙም፡፡
فِيهَا عَيْنٌۭ جَارِيَةٌۭ
በውስጧ ፈሳሾች ምንጮች አልሉ፡፡
فِيهَا سُرُرٌۭ مَّرْفُوعَةٌۭ
በውስጧ ከፍ የተደረጉ አልጋዎች አልሉ፡፡
وَأَكْوَابٌۭ مَّوْضُوعَةٌۭ
በተርታ የተኖሩ ብርጭቆዎችም፡፡
وَنَمَارِقُ مَصْفُوفَةٌۭ
የተደረደሩ መከዳዎችም፡፡
وَزَرَابِىُّ مَبْثُوثَةٌ
የተነጠፉ ስጋጃዎችም (አልሉ)፡፡
أَفَلَا يَنظُرُونَ إِلَى ٱلْإِبِلِ كَيْفَ خُلِقَتْ
(ከሓዲዎች) አይመለከቱምን? ወደ ግመል እንዴት እነደተፈጠረች!
وَإِلَى ٱلسَّمَآءِ كَيْفَ رُفِعَتْ
ወደ ሰማይም እንዴት ከፍ እንደ ተደረገች!
وَإِلَى ٱلْجِبَالِ كَيْفَ نُصِبَتْ
ወደ ተራራዎችም እንዴት እንደ ተቸከሉ!
وَإِلَى ٱلْأَرْضِ كَيْفَ سُطِحَتْ
ወደ ምድርም እንዴ እንደተዘረጋች (አይመለከቱምን?)
فَذَكِّرْ إِنَّمَآ أَنتَ مُذَكِّرٌۭ
አስታውስም፤ አንተ አስታዋሽ ብቻ ነህና፡፡
لَّسْتَ عَلَيْهِم بِمُصَيْطِرٍ
በእነርሱ ላይ ተሿሚ (አስገዳጅ) አይደለህም፡፡
إِلَّا مَن تَوَلَّىٰ وَكَفَرَ
ግን (ከእውነት) የዞረና የካደ ሰው፤
فَيُعَذِّبُهُ ٱللَّهُ ٱلْعَذَابَ ٱلْأَكْبَرَ
አላህ ታላቁን ቅጣት ይቀጣዋል፡፡
إِنَّ إِلَيْنَآ إِيَابَهُمْ
መመለሻቸው ወደእኛ ብቻ ነው፡፡
ثُمَّ إِنَّ عَلَيْنَا حِسَابَهُم
ከዚያም ምርመራቸው በእኛ ላይ ብቻ ነው፡፡
Surah 89: Al-Fajr — الفجر
وَٱلْفَجْرِ
በጎህ እምላለሁ፡፡
وَلَيَالٍ عَشْرٍۢ
በዐሥር ሌሊቶችም፡፡
وَٱلشَّفْعِ وَٱلْوَتْرِ
በጥንዱም በነጠላውም፡፡
وَٱلَّيْلِ إِذَا يَسْرِ
በሌሊቱም በሚኼድ ጊዜ፡፡
هَلْ فِى ذَٰلِكَ قَسَمٌۭ لِّذِى حِجْرٍ
በዚህ (መሓላ) ለባለ አእምሮ ታላቅ መሓላ አለበትን?
أَلَمْ تَرَ كَيْفَ فَعَلَ رَبُّكَ بِعَادٍ
ጌታህ በዓድ እንዴት እንደ ሠራ አታውቅምን?
إِرَمَ ذَاتِ ٱلْعِمَادِ
በኢረም በባለ ረዣዢሚቱ አዕማድ፡፡
ٱلَّتِى لَمْ يُخْلَقْ مِثْلُهَا فِى ٱلْبِلَٰدِ
በዚያች ብጤዋ በአገሮች ውስጥ ያልተፈጠረ በኾነችው፡፡
وَثَمُودَ ٱلَّذِينَ جَابُوا۟ ٱلصَّخْرَ بِٱلْوَادِ
በሰሙድም በእነዚያ በሸለቆው ቋጥኝን የቆረጡ በኾኑት፡፡
وَفِرْعَوْنَ ذِى ٱلْأَوْتَادِ
በፈርዖንም ባለ ችካሎች በኾነው፡፡
ٱلَّذِينَ طَغَوْا۟ فِى ٱلْبِلَٰدِ
በእነዚያ በአገሮች ላይ ግፍ የሠሩ፡፡
فَأَكْثَرُوا۟ فِيهَا ٱلْفَسَادَ
በእርሷም ውስጥ ጥፋትን ያበዙ በኾኑት (እንዴት እንደሠራ አታውቅምን?)
فَصَبَّ عَلَيْهِمْ رَبُّكَ سَوْطَ عَذَابٍ
በእነርሱ ላይም ጌታህ የቅጣትን አለንጋ አወረደባቸው፡፡
إِنَّ رَبَّكَ لَبِٱلْمِرْصَادِ
ጌታህ በመጠባበቂያ ላይ ነውና፡፡
فَأَمَّا ٱلْإِنسَٰنُ إِذَا مَا ٱبْتَلَىٰهُ رَبُّهُۥ فَأَكْرَمَهُۥ وَنَعَّمَهُۥ فَيَقُولُ رَبِّىٓ أَكْرَمَنِ
ሰውማ ጌታው በሞከረው ጊዜ፣ ባከበረውና ባጣቀመውም (ጊዜ) «ጌታዬ አከበረኝ (አበለጠኝ)» ይላል፡፡
وَأَمَّآ إِذَا مَا ٱبْتَلَىٰهُ فَقَدَرَ عَلَيْهِ رِزْقَهُۥ فَيَقُولُ رَبِّىٓ أَهَٰنَنِ
በሞከረውና በእርሱ ላይ ሲሳዩን ባጠበበ ጊዜማ «ጌታዬ አሳነሰኝ» ይላል፡፡
كَلَّا ۖ بَل لَّا تُكْرِمُونَ ٱلْيَتِيمَ
ይከልከል፤ ይልቁንም የቲምን አታከብሩም፡፡
وَلَا تَحَٰٓضُّونَ عَلَىٰ طَعَامِ ٱلْمِسْكِينِ
ድኻንም በማብላት ላይ አትታዘዙም፡፡
وَتَأْكُلُونَ ٱلتُّرَاثَ أَكْلًۭا لَّمًّۭا
የውርስንም ገንዘብ የመሰብሰብን አበላል ትበላላችሁ፡፡
وَتُحِبُّونَ ٱلْمَالَ حُبًّۭا جَمًّۭا
ገንዘብንም ብዙን መውደድ ትወዳላችሁ፡፡
كَلَّآ إِذَا دُكَّتِ ٱلْأَرْضُ دَكًّۭا دَكًّۭا
ተዉ፤ ምድር ደጋግማ በተሰባበረች ጊዜ፤
وَجَآءَ رَبُّكَ وَٱلْمَلَكُ صَفًّۭا صَفًّۭا
መላእክትም ሰልፍ ሰልፍ ኾነው ጌታህ (ትዕዛዙ) በመጣ ጊዜ፤
وَجِا۟ىٓءَ يَوْمَئِذٍۭ بِجَهَنَّمَ ۚ يَوْمَئِذٍۢ يَتَذَكَّرُ ٱلْإِنسَٰنُ وَأَنَّىٰ لَهُ ٱلذِّكْرَىٰ
ገሀነምም በዚያ ቀን በተመጣች ጊዜ በዚያ ቀን ሰው (ጥፋቱን) ይገነዘባል፡፡ መገንዘብም ለእርሱ ከየቱ?
يَقُولُ يَٰلَيْتَنِى قَدَّمْتُ لِحَيَاتِى
«ዋ እኔ! ምነው በሕይወቴ (መልካምን ሥራ) ባስቀደምኩ ኖሮ» ይላል፡፡
فَيَوْمَئِذٍۢ لَّا يُعَذِّبُ عَذَابَهُۥٓ أَحَدٌۭ
በዚያ ቀንም የርሱን አቀጣጥ አንድም አይቀጣም፡፡
وَلَا يُوثِقُ وَثَاقَهُۥٓ أَحَدٌۭ
የእርሱንም አስተሳሰር አንድም አያስርም፡፡
يَٰٓأَيَّتُهَا ٱلنَّفْسُ ٱلْمُطْمَئِنَّةُ
(ለአመነች ነፍስም) «አንቺ የረካሺው ነፍስ ሆይ!
ٱرْجِعِىٓ إِلَىٰ رَبِّكِ رَاضِيَةًۭ مَّرْضِيَّةًۭ
«ወዳጅ ተወዳጅ ኾነሽ ወደ ጌታሽ ተመለሺ፡፡
فَٱدْخُلِى فِى عِبَٰدِى
«በባሮቼም ውስጥ ግቢ፡፡
وَٱدْخُلِى جَنَّتِى
ገነቴንም ግቢ፤» (ትባላለች)፡፡
Surah 90: Al-Balad — البلد
لَآ أُقْسِمُ بِهَٰذَا ٱلْبَلَدِ
በዚህ አገር (በመካ) እምላለሁ፡፡
وَأَنتَ حِلٌّۢ بِهَٰذَا ٱلْبَلَدِ
አንተ በዚህ አገር ሰፋሪ ስትኾን፡፡
وَوَالِدٍۢ وَمَا وَلَدَ
በወላጂም በወለዳቸውም ሰዎች (በአዳምና በዘሮቹ ሁሉ እምላለሁ)፡፡
لَقَدْ خَلَقْنَا ٱلْإِنسَٰنَ فِى كَبَدٍ
ሰውን ሁሉ በእርግጥ በልፋት ውስጥ ኾኖ ፈጠርነው፡፡
أَيَحْسَبُ أَن لَّن يَقْدِرَ عَلَيْهِ أَحَدٌۭ
በእርሱ ላይ አንድም የማይችል መኾኑን ይጠረጥራልን?
يَقُولُ أَهْلَكْتُ مَالًۭا لُّبَدًا
«ብዙን ገንዘብ አጠፋሁ» ይላል፡፡
أَيَحْسَبُ أَن لَّمْ يَرَهُۥٓ أَحَدٌ
አንድም ያላየው መኾኑን ያስባልን?
أَلَمْ نَجْعَل لَّهُۥ عَيْنَيْنِ
ለእርሱ ሁለት ዓይኖችን አላደረግንለትምን?
وَلِسَانًۭا وَشَفَتَيْنِ
ምላስንና ሁለት ከንፈሮችንም፡፡
وَهَدَيْنَٰهُ ٱلنَّجْدَيْنِ
ሁለትን መንገዶችም አልመራነውምን?
فَلَا ٱقْتَحَمَ ٱلْعَقَبَةَ
ዓቀበቲቱንም አልወጣም፡፡
وَمَآ أَدْرَىٰكَ مَا ٱلْعَقَبَةُ
ዓቀበቲቱም (መውጣቷ) ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?
فَكُّ رَقَبَةٍ
(እርሱ) ጫንቃን መልቀቅ ነው፡፡
أَوْ إِطْعَٰمٌۭ فِى يَوْمٍۢ ذِى مَسْغَبَةٍۢ
ወይም የረኃብ ባለቤት በኾነ ቀን ማብላት፡፡
يَتِيمًۭا ذَا مَقْرَبَةٍ
የዝምድና ባለቤት የኾነን የቲም፤
أَوْ مِسْكِينًۭا ذَا مَتْرَبَةٍۢ
ወይም የዐፈር ባለቤት የኾነን ድኻ (ማብላት ነው)፡፡
ثُمَّ كَانَ مِنَ ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ وَتَوَاصَوْا۟ بِٱلصَّبْرِ وَتَوَاصَوْا۟ بِٱلْمَرْحَمَةِ
(ዐቀበቲቱን አልወጣም)፡፡ ከዚያም ከነዚያ ከአመኑትና በመታገስ አደራ ከተባባሉት፣ በማዘንም አደራ ከተባባሉት ሰዎች አልኾነም፡፡
أُو۟لَٰٓئِكَ أَصْحَٰبُ ٱلْمَيْمَنَةِ
እነዚያ (ይህንን የፈጸሙ) የቀኝ ጓዶች ናቸው፡፡
وَٱلَّذِينَ كَفَرُوا۟ بِـَٔايَٰتِنَا هُمْ أَصْحَٰبُ ٱلْمَشْـَٔمَةِ
እነዚያም በአንቀጾቻችን የካዱት እነርሱ የግራ ጓዶች ናቸው፡፡
عَلَيْهِمْ نَارٌۭ مُّؤْصَدَةٌۢ
በእነርሱ ላይ የተዘጋች እሳት አልለች፡፡
Surah 91: Ash-Shams — الشمس
وَٱلشَّمْسِ وَضُحَىٰهَا
በፀሐይና በብርሃኗ እምላለሁ፡፡
وَٱلْقَمَرِ إِذَا تَلَىٰهَا
በጨረቃም በተከተላት ጊዜ፤
وَٱلنَّهَارِ إِذَا جَلَّىٰهَا
በቀኑም (ፀሐይን) በገለጻት ጊዜ፤
وَٱلَّيْلِ إِذَا يَغْشَىٰهَا
በሌሊቱም በሸፈናት ጊዜ፤
وَٱلسَّمَآءِ وَمَا بَنَىٰهَا
በሰማይቱም በገነባትም (ጌታ)፤
وَٱلْأَرْضِ وَمَا طَحَىٰهَا
በምድሪቱም በዘረጋትም፤
وَنَفْسٍۢ وَمَا سَوَّىٰهَا
በነፍስም ባስተካከላትም፤
فَأَلْهَمَهَا فُجُورَهَا وَتَقْوَىٰهَا
አመጽዋንና ፍርሃትዋንም ባሳወቃት (አምላክ እምላለሁ)፡፡
قَدْ أَفْلَحَ مَن زَكَّىٰهَا
(ከኀጢኣት) ያጠራት ሰው ፍላጎቱን በእርግጥ አገኘ፡፡
وَقَدْ خَابَ مَن دَسَّىٰهَا
(በኀጢኣት) የሸፈናትም ሰው በእውነት አፈረ፡፡
كَذَّبَتْ ثَمُودُ بِطَغْوَىٰهَآ
ሠሙድ ወሰን በማለፍዋ አስተባበለች፡፡
إِذِ ٱنۢبَعَثَ أَشْقَىٰهَا
ጠማማዋ በተንቀሳቀሰ ጊዜ፡፡
فَقَالَ لَهُمْ رَسُولُ ٱللَّهِ نَاقَةَ ٱللَّهِ وَسُقْيَٰهَا
ለእነርሱም የአላህ መልክተኛ (ሷሊህ) «የአላህን ግመል የመጠጥ ተራዋንም (ተጠንቀቁ)» አላቸው፡፡
فَكَذَّبُوهُ فَعَقَرُوهَا فَدَمْدَمَ عَلَيْهِمْ رَبُّهُم بِذَنۢبِهِمْ فَسَوَّىٰهَا
አስተባበሉትም፡፡ (ቋንጃዋን) ወጓትም፡፡ በኀጢኣታቸውም ምክንያት ጌታቸው (ቅጣትን) በእነርሱ ላይ ደመደመባቸው፤ አስተካከላትም፡፡
وَلَا يَخَافُ عُقْبَٰهَا
ፍጻሜዋንም (የምታስከትለውን) አያፈራም፡፡
Surah 92: Al-Lail — الليل
وَٱلَّيْلِ إِذَا يَغْشَىٰ
በሌሊቱ እምላለሁ (በጨለማው) በሚሸፍን ጊዜ፡፡
وَٱلنَّهَارِ إِذَا تَجَلَّىٰ
በቀኑም፤ በተገለጸ ጊዜ፡፡
وَمَا خَلَقَ ٱلذَّكَرَ وَٱلْأُنثَىٰٓ
ወንድንና ሴትን በፈጠረውም (አምላክ እምላለሁ)፡፡
إِنَّ سَعْيَكُمْ لَشَتَّىٰ
ሥራችሁ በእርግጥ የተለያየ ነው፡፡
فَأَمَّا مَنْ أَعْطَىٰ وَٱتَّقَىٰ
የሰጠ ሰውማ ጌታውን የፈራም፡፡
وَصَدَّقَ بِٱلْحُسْنَىٰ
በመልካሚቱም (እምነት) ያረጋገጠ፤
فَسَنُيَسِّرُهُۥ لِلْيُسْرَىٰ
ለገሪቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡
وَأَمَّا مَنۢ بَخِلَ وَٱسْتَغْنَىٰ
የሰሰተ ሰውማ የተብቃቃም፤ (በራሱ የተመካ)፤
وَكَذَّبَ بِٱلْحُسْنَىٰ
በመልካሚቱ (እምነት) ያሰተባበለም፤
فَسَنُيَسِّرُهُۥ لِلْعُسْرَىٰ
ለክፉይቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡
وَمَا يُغْنِى عَنْهُ مَالُهُۥٓ إِذَا تَرَدَّىٰٓ
በወደቀም ጊዜ ገንዘቡ ከእርሱ ምንም አይጠቅመውም፡፡
إِنَّ عَلَيْنَا لَلْهُدَىٰ
ቅኑን መንገድ መግለጽ በእኛ ላይ አለብን፡፡
وَإِنَّ لَنَا لَلْءَاخِرَةَ وَٱلْأُولَىٰ
መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም ዓለም የእኛ ናቸው፡፡
فَأَنذَرْتُكُمْ نَارًۭا تَلَظَّىٰ
የምትንቀለቀልንም እሳት አስጠነቀቅኳችሁ (በላቸው)፡፡
لَا يَصْلَىٰهَآ إِلَّا ٱلْأَشْقَى
ከጠማማ በቀር ሌላ የማይገባት የኾነችን፡፡
ٱلَّذِى كَذَّبَ وَتَوَلَّىٰ
ያ ያስተባበለና ከትዕዛዝ የሸሸው፡፡
وَسَيُجَنَّبُهَا ٱلْأَتْقَى
አላህን በጣም ፈሪውም በእርግጥ ይርቃታል፡፡
ٱلَّذِى يُؤْتِى مَالَهُۥ يَتَزَكَّىٰ
ያ የሚጥራራ ኾኖ ገንዘቡን (ለድኾች) የሚሰጠው፡፡
وَمَا لِأَحَدٍ عِندَهُۥ مِن نِّعْمَةٍۢ تُجْزَىٰٓ
ለአንድም ሰው እርሱ ዘንድ የምትመለስ ውለታ የለችም፡፡
إِلَّا ٱبْتِغَآءَ وَجْهِ رَبِّهِ ٱلْأَعْلَىٰ
ግን የታላቅ ጌታውን ውዴታ ለመፈለግ (ይህንን ሠራ)፡፡
وَلَسَوْفَ يَرْضَىٰ
ወደፊትም በእርግጥ ይደሰታል፡፡
Surah 93: Ad-Duha — الضحى
وَٱلضُّحَىٰ
በረፋዱ እምላለሁ፡፡
وَٱلَّيْلِ إِذَا سَجَىٰ
በሌሊቱም ጸጥ ባለ ጊዜ፤
مَا وَدَّعَكَ رَبُّكَ وَمَا قَلَىٰ
ጌታህ አላሰናበተህም፤ አልጠላህምም፡፡
وَلَلْءَاخِرَةُ خَيْرٌۭ لَّكَ مِنَ ٱلْأُولَىٰ
መጨረሻይቱም (ዓለም) ከመጀመሪያይቱ ይልቅ ላንተ በላጭ ናት፡፡
وَلَسَوْفَ يُعْطِيكَ رَبُّكَ فَتَرْضَىٰٓ
ጌታህም ወደ ፊት (ብዙን ስጦታ) በእርግጥ ይሰጥሃል፡፡ ትደሰታለህም፡፡
أَلَمْ يَجِدْكَ يَتِيمًۭا فَـَٔاوَىٰ
የቲም ኾነህ አላገኘህምና አላስጠጋህምን? (አስጠግቶሃል)፡፡
وَوَجَدَكَ ضَآلًّۭا فَهَدَىٰ
የሳትክም ኾነህ አገኘህ መራህም፡፡
وَوَجَدَكَ عَآئِلًۭا فَأَغْنَىٰ
ድኻም ኾነህ አገኘህ፤ አከበረህም፡፡
فَأَمَّا ٱلْيَتِيمَ فَلَا تَقْهَرْ
የቲምንማ አትጨቁን፡፡
وَأَمَّا ٱلسَّآئِلَ فَلَا تَنْهَرْ
ለማኝንም አትገላምጥ፡፡
وَأَمَّا بِنِعْمَةِ رَبِّكَ فَحَدِّثْ
በጌታህም ጸጋ አውራ፤ (ግለጻት)፡፡
Surah 94: Ash-Sharh — الشرح
أَلَمْ نَشْرَحْ لَكَ صَدْرَكَ
ልብህን ለአንተ አላሰፋንልህምን? (አስፍተንልሃል)፡፡
وَوَضَعْنَا عَنكَ وِزْرَكَ
ሸክምህንም ካንተ አውርደንልሃል፡፡
ٱلَّذِىٓ أَنقَضَ ظَهْرَكَ
ያንን ጀርባህን ያከበደውን (ሸክም)፡፡
وَرَفَعْنَا لَكَ ذِكْرَكَ
መወሳትህንም ላንተ ከፍ አድርገንልሃል፡፡
فَإِنَّ مَعَ ٱلْعُسْرِ يُسْرًا
ከችግርም ጋር ምቾት አልለ፡፡
إِنَّ مَعَ ٱلْعُسْرِ يُسْرًۭا
ከችግር ጋር በእርግጥ ምቾት አልለ፡፡
فَإِذَا فَرَغْتَ فَٱنصَبْ
በጨረስክም ጊዜ ልፋ፡፡ (ቀጥል)፡፡
وَإِلَىٰ رَبِّكَ فَٱرْغَب
ወደ ጌታህም ብቻ ከጅል፡፡
Surah 95: At-Tin — التين
وَٱلتِّينِ وَٱلزَّيْتُونِ
በበለስና በዘይት ወይራ እምላለሁ፡፡
وَطُورِ سِينِينَ
በሲኒን ተራራም፤
وَهَٰذَا ٱلْبَلَدِ ٱلْأَمِينِ
በዚህ በጸጥተኛው አገርም (እምላለሁ)፡፡
لَقَدْ خَلَقْنَا ٱلْإِنسَٰنَ فِىٓ أَحْسَنِ تَقْوِيمٍۢ
ሰውን በጣም በአማረ አቋም ላይ ፈጠርነው፡፡
ثُمَّ رَدَدْنَٰهُ أَسْفَلَ سَٰفِلِينَ
ከዚያም (ከፊሉን) ከዝቅተኞች ሁሉ በታች አድርገን መለስነው፡፡
إِلَّا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ وَعَمِلُوا۟ ٱلصَّٰلِحَٰتِ فَلَهُمْ أَجْرٌ غَيْرُ مَمْنُونٍۢ
ግን እነዚያ ያመኑት መልካሞችንም የሠሩት ለእነርሱ ተቆራጭ ያልኾነ ምንዳ አልላቸው፡፡
فَمَا يُكَذِّبُكَ بَعْدُ بِٱلدِّينِ
ታዲያ ከዚህ በኋላ በፍርዱ ምን አስተባባይ አደረገህ?
أَلَيْسَ ٱللَّهُ بِأَحْكَمِ ٱلْحَٰكِمِينَ
አላህ ከፈራጆች ሁሉ ይበልጥ ፈራጅ አይደለምን? (ነው)፡፡
Surah 96: Al-Alaq — العلق
ٱقْرَأْ بِٱسْمِ رَبِّكَ ٱلَّذِى خَلَقَ
አንብብ በዚያ (ሁሉን) በፈጠረው ጌታህ ስም፡፡
خَلَقَ ٱلْإِنسَٰنَ مِنْ عَلَقٍ
ሰውን ከረጋ ደም በፈጠረው (ጌታህ ስም)፡፡
ٱقْرَأْ وَرَبُّكَ ٱلْأَكْرَمُ
አንብብ፤ ጌታህ በጣም ቸር ሲኾን፤
ٱلَّذِى عَلَّمَ بِٱلْقَلَمِ
ያ በብርዕ ያስተማረ፡፡
عَلَّمَ ٱلْإِنسَٰنَ مَا لَمْ يَعْلَمْ
ሰውን ያላወቀውን ሁሉ ያሳወቀ ሲኾን፡፡
كَلَّآ إِنَّ ٱلْإِنسَٰنَ لَيَطْغَىٰٓ
በእውነቱ ሰው ወሰንን ያልፋል፡፡
أَن رَّءَاهُ ٱسْتَغْنَىٰٓ
ራሱን የተብቃቃ (ባለ ሀብት) ኾኖ ለማየቱ፡፡
إِنَّ إِلَىٰ رَبِّكَ ٱلرُّجْعَىٰٓ
መመለሻው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
أَرَءَيْتَ ٱلَّذِى يَنْهَىٰ
አየህን? ያንን የሚከለክለውን፡፡
عَبْدًا إِذَا صَلَّىٰٓ
ባሪያን በሰገደ ጊዜ፤
أَرَءَيْتَ إِن كَانَ عَلَى ٱلْهُدَىٰٓ
አየህን? ንገረኝ (ተከልካዩ) በትክክለኛ መንገድ ላይ ቢኾን፤
أَوْ أَمَرَ بِٱلتَّقْوَىٰٓ
ወይም (ፈጣሪውን) በመፍራት ቢያዝ፤
أَرَءَيْتَ إِن كَذَّبَ وَتَوَلَّىٰٓ
አየህን? ንገረኝ (ከልካዩ) ቢያስተባብልና (ከእምነት) ቢሸሽ፤
أَلَمْ يَعْلَم بِأَنَّ ٱللَّهَ يَرَىٰ
አላህ የሚያይ መኾኑን አያውቅምን?
كَلَّا لَئِن لَّمْ يَنتَهِ لَنَسْفَعًۢا بِٱلنَّاصِيَةِ
ይተው ባይከለከል አናቱን ይዘን እንጎትተዋለን፡፡
نَاصِيَةٍۢ كَٰذِبَةٍ خَاطِئَةٍۢ
ውሸታም ስሕተተኛ የኾነችውን አናቱን፡፡
فَلْيَدْعُ نَادِيَهُۥ
ሸንጎውንም ይጥራ፡፡
سَنَدْعُ ٱلزَّبَانِيَةَ
(እኛም) ዘበኞቻችንን እንጠራለን፡፡
كَلَّا لَا تُطِعْهُ وَٱسْجُدْ وَٱقْتَرِب ۩
ይከልከል አትታዘዘው፡፡ ስገድም፤ (ወደ አላህ) ተቃረብም፡፡
Surah 97: Al-Qadr — القدر
إِنَّآ أَنزَلْنَٰهُ فِى لَيْلَةِ ٱلْقَدْرِ
እኛ (ቁርኣኑን) በመወሰኛይቱ ሌሊት አወረድነው፡፡
وَمَآ أَدْرَىٰكَ مَا لَيْلَةُ ٱلْقَدْرِ
መወሰኛይቱም ሌሊተ ምን እንደ ኾነች ምን አሳወቀህ?
لَيْلَةُ ٱلْقَدْرِ خَيْرٌۭ مِّنْ أَلْفِ شَهْرٍۢ
መወሰኛይቱ ሌሊት ከሺሕ ወር በላጭ ናት፡፡
تَنَزَّلُ ٱلْمَلَٰٓئِكَةُ وَٱلرُّوحُ فِيهَا بِإِذْنِ رَبِّهِم مِّن كُلِّ أَمْرٍۢ
በርሷ ውስጥ መላእክትና መንፈሱ በጌታቸው ፈቃድ በነገሩ ሁሉ ይወርዳሉ፡፡
سَلَٰمٌ هِىَ حَتَّىٰ مَطْلَعِ ٱلْفَجْرِ
እርስዋ እስከ ጎህ መውጣት ድረስ ሰላም ብቻ ናት፡፡
Surah 98: Al-Bayinah — البينة
لَمْ يَكُنِ ٱلَّذِينَ كَفَرُوا۟ مِنْ أَهْلِ ٱلْكِتَٰبِ وَٱلْمُشْرِكِينَ مُنفَكِّينَ حَتَّىٰ تَأْتِيَهُمُ ٱلْبَيِّنَةُ
እነዚያ ከመጽሐፉ ባለቤቶች ከአጋሪዎቹም የካዱት ግልጹ አስረጅ እስከ መጣላቸው ድረስ (ከነበሩበት ላይ) ተወጋጆች አልነበሩም፡፡
رَسُولٌۭ مِّنَ ٱللَّهِ يَتْلُوا۟ صُحُفًۭا مُّطَهَّرَةًۭ
(አስረጁም) ከአላህ የኾነ መልክተኛ የተጥራሩን መጽሐፎች የሚያነብ ነው፡፡
فِيهَا كُتُبٌۭ قَيِّمَةٌۭ
በውስጧ ቀጥተኛ የኾኑ ጽሑፎች ያሉባት የኾነችን፡፡
وَمَا تَفَرَّقَ ٱلَّذِينَ أُوتُوا۟ ٱلْكِتَٰبَ إِلَّا مِنۢ بَعْدِ مَا جَآءَتْهُمُ ٱلْبَيِّنَةُ
እነዚያም መጽሐፉን የተሰጡት ሰዎች ግልጽ አስረጅ ከመጣላቸው በኋላ እንጅ አልተለያዩም፡፡
وَمَآ أُمِرُوٓا۟ إِلَّا لِيَعْبُدُوا۟ ٱللَّهَ مُخْلِصِينَ لَهُ ٱلدِّينَ حُنَفَآءَ وَيُقِيمُوا۟ ٱلصَّلَوٰةَ وَيُؤْتُوا۟ ٱلزَّكَوٰةَ ۚ وَذَٰلِكَ دِينُ ٱلْقَيِّمَةِ
አላህን ሃይማኖትን ለእርሱ ብቻ አጥሪዎች፣ ቀጥተኞች ኾነው ሊግገዙት፣ ሶላትንም አስተካክለው ሊሰግዱ ዘካንም ሊሰጡ እንጅ ያልታዘዙ ሲኾኑ (ተለያዩ)፡፡ ይህም የቀጥተኛይቱ (ሃይማኖት) ድንጋጌ ነው፡፡
إِنَّ ٱلَّذِينَ كَفَرُوا۟ مِنْ أَهْلِ ٱلْكِتَٰبِ وَٱلْمُشْرِكِينَ فِى نَارِ جَهَنَّمَ خَٰلِدِينَ فِيهَآ ۚ أُو۟لَٰٓئِكَ هُمْ شَرُّ ٱلْبَرِيَّةِ
እነዚያ ከመጽሐፉ ሰዎች የካዱት፣ አጋሪዎቹም በገሀነም እሳት ውስጥ ናቸው፤ በውስጧ ዘውታሪዎች ሲኾኑ እነዚያ እነርሱ ከፍጥረት ሁሉ ክፉ ናቸው፡፡
إِنَّ ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ وَعَمِلُوا۟ ٱلصَّٰلِحَٰتِ أُو۟لَٰٓئِكَ هُمْ خَيْرُ ٱلْبَرِيَّةِ
እነዚያ ያመኑትና መልካሞችንም የሠሩት፣ እነዚያ እነርሱ ከፍጥረት ሁሉ በላጭ ናቸው፡፡
جَزَآؤُهُمْ عِندَ رَبِّهِمْ جَنَّٰتُ عَدْنٍۢ تَجْرِى مِن تَحْتِهَا ٱلْأَنْهَٰرُ خَٰلِدِينَ فِيهَآ أَبَدًۭا ۖ رَّضِىَ ٱللَّهُ عَنْهُمْ وَرَضُوا۟ عَنْهُ ۚ ذَٰلِكَ لِمَنْ خَشِىَ رَبَّهُۥ
በጌታቸው ዘንድ ምንዳቸው ከሥሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው የመኖሪያ ገነቶች ነው፡፡ በውስጣቸው ዘለዓለም ዘውታሪዎች ሲኾኑ (ይገቡባቸወል)፡፡ አላህ ከእነርሱ ወደደ፡፡ ከእርሱም ወደዱ፡፡ ይህ ጌታውን ለፈራ ሰው ነው፡፡
Surah 99: Az-Zalzalah — الزلزلة
إِذَا زُلْزِلَتِ ٱلْأَرْضُ زِلْزَالَهَا
ምድር (በኀይል) መንቀጥቀጥዋን በተንቀጠቀጠች ጊዜ፤
وَأَخْرَجَتِ ٱلْأَرْضُ أَثْقَالَهَا
ምድር ሸክሞችዋን ባወጣችም ጊዜ፤
وَقَالَ ٱلْإِنسَٰنُ مَا لَهَا
ሰውም ምን ኾነች? ባለ ጊዜ፤
يَوْمَئِذٍۢ تُحَدِّثُ أَخْبَارَهَا
በዚያ ቀን ወሬዎችዋን ትናገራለች፡፡
بِأَنَّ رَبَّكَ أَوْحَىٰ لَهَا
ጌታህ ለእርሷ በማሳወቁ ምክንያት፡፡
يَوْمَئِذٍۢ يَصْدُرُ ٱلنَّاسُ أَشْتَاتًۭا لِّيُرَوْا۟ أَعْمَٰلَهُمْ
በዚያ ቀን ሰዎች ሥራዎቻቸውን (ምንዳዋን) እንዲያዩ ይደረጉ ዘንድ (እንደየሥራቸው) የተለያዩ ኾነው (ከመቆሚያው ስፍራ) ይመለሳሉ፡፡
فَمَن يَعْمَلْ مِثْقَالَ ذَرَّةٍ خَيْرًۭا يَرَهُۥ
የብናኝ ክብደት ያክልም መልካምን የሠራ ሰው ያገኘዋል፡፡
وَمَن يَعْمَلْ مِثْقَالَ ذَرَّةٍۢ شَرًّۭا يَرَهُۥ
የብናኝ ክብደት ያክልም ክፉን የሠራ ሰው ያገኘዋል፡፡
Surah 100: Al-Adiyat — العاديات
وَٱلْعَٰدِيَٰتِ ضَبْحًۭا
እያለከለኩ ሩዋጮች በኾኑት (ፈረሶች) እምላለሁ፡፡
فَٱلْمُورِيَٰتِ قَدْحًۭا
(በሰኮናቸው) እያጋጩ እሳትን አውጪዎች በኾኑትም፤
فَٱلْمُغِيرَٰتِ صُبْحًۭا
በማለዳ ወራሪዎች በኾኑትም፤
فَأَثَرْنَ بِهِۦ نَقْعًۭا
በእርሱ አቧራን በቀሰቀሱትም፤
فَوَسَطْنَ بِهِۦ جَمْعًا
በ(ጠላት) ክቢ መካከል በእርሱ (በጧት) በተጋፈጡትም እምላለሁ፡፡
إِنَّ ٱلْإِنسَٰنَ لِرَبِّهِۦ لَكَنُودٌۭ
ሰው ለጌታው ብርቱ ከሓዲ ነው፡፡
وَإِنَّهُۥ عَلَىٰ ذَٰلِكَ لَشَهِيدٌۭ
እርሱም በዚህ ላይ መስካሪ ነው፡፡
وَإِنَّهُۥ لِحُبِّ ٱلْخَيْرِ لَشَدِيدٌ
እርሱም ገንዘብን ለመውደድ በጣም ብርቱ ነው፡፡
۞ أَفَلَا يَعْلَمُ إِذَا بُعْثِرَ مَا فِى ٱلْقُبُورِ
(ሰው) አያውቅምን? በመቃብሮች ያሉት (ሙታን) በተቀሰቀሱ ጊዜ፤
وَحُصِّلَ مَا فِى ٱلصُّدُورِ
በልቦች ውስጥ ያለውም ሁሉ በተገለጸ ጊዜ (እንዴት እንደሚኾን)፡፡
إِنَّ رَبَّهُم بِهِمْ يَوْمَئِذٍۢ لَّخَبِيرٌۢ
ጌታቸው በዚያ ቀን በእነርሱ (ነገር) በእርግጥ ውስጠ አዋቂ ነው፡፡
Surah 101: Al-Qariah — القارعة
ٱلْقَارِعَةُ
ቆርቋሪይቱ (ጩኸት)፤
مَا ٱلْقَارِعَةُ
ምን አስደናቂ ቆርቋሪ ናት!
وَمَآ أَدْرَىٰكَ مَا ٱلْقَارِعَةُ
ቆርቋሪይቱም ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?
يَوْمَ يَكُونُ ٱلنَّاسُ كَٱلْفَرَاشِ ٱلْمَبْثُوثِ
ሰዎች እንደ ተበታተነ ቢራቢሮ (ወይም ኩብኩባ) በሚኾኑበት ቀን፤
وَتَكُونُ ٱلْجِبَالُ كَٱلْعِهْنِ ٱلْمَنفُوشِ
ጋራዎችም እንደ ተነደፈ ሱፍ በሚኾኑበት (ቀን ልቦችን በድንጋጤ ትቆረቁራለች፡፡)
فَأَمَّا مَن ثَقُلَتْ مَوَٰزِينُهُۥ
ሚዛኖቹ የከበዱለት ሰውማ፤
فَهُوَ فِى عِيشَةٍۢ رَّاضِيَةٍۢ
እርሱ በምትወደድ ኑሮ ውስጥ ይኾናል፡፡
وَأَمَّا مَنْ خَفَّتْ مَوَٰزِينُهُۥ
ሚዛኖቹም የቀለሉበት ሰውማ፤
فَأُمُّهُۥ هَاوِيَةٌۭ
መኖሪያው ሃዊያህ ናት
وَمَآ أَدْرَىٰكَ مَا هِيَهْ
እርሷም ምን እንደ ኾነች ምን አሳወቀህ?
نَارٌ حَامِيَةٌۢ
(እርሷ) በጣም ተኳሳ እሳት ናት፡፡
Surah 102: Al-Takathur — التكاثر
أَلْهَىٰكُمُ ٱلتَّكَاثُرُ
በብዛት መፎካከር (ጌታችሁን ከመገዛት) አዘነጋችሁ፡፡
حَتَّىٰ زُرْتُمُ ٱلْمَقَابِرَ
መቃብሮችን እስከ ጎበኛችሁ ድረስ፡፡
كَلَّا سَوْفَ تَعْلَمُونَ
ተከልከሉ፤ ወደፊት (ውጤቱን) ታውቃላችሁ፡፡
ثُمَّ كَلَّا سَوْفَ تَعْلَمُونَ
ከዚያም ተከልከሉ፤ ወደ ፊት ታውቃላችሁ፡፡
كَلَّا لَوْ تَعْلَمُونَ عِلْمَ ٱلْيَقِينِ
በእውነቱ (የሚጠብቃችሁን) እርግጠኛ ዕውቀትን ብታውቁ ኖሮ፤ (ባልዘናጋችሁ ነበር)፡፡
لَتَرَوُنَّ ٱلْجَحِيمَ
ገሀነምን በእርግጥ ታያላችሁ፡፡
ثُمَّ لَتَرَوُنَّهَا عَيْنَ ٱلْيَقِينِ
ከዚያም እርግጠኛን ማየት ታዩዋታላችሁ፡፡
ثُمَّ لَتُسْـَٔلُنَّ يَوْمَئِذٍ عَنِ ٱلنَّعِيمِ
ከዚያም ከድሎታችሁ ሁሉ በዚያ ቀን ትጠየቃላችሁ፡፡
Surah 103: Al-Asr — العصر
وَٱلْعَصْرِ
በጊዜያቱ እምላለሁ፡፡
إِنَّ ٱلْإِنسَٰنَ لَفِى خُسْرٍ
ሰው ሁሉ በእርግጥ በከሳራ ውስጥ ነው፡፡
إِلَّا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ وَعَمِلُوا۟ ٱلصَّٰلِحَٰتِ وَتَوَاصَوْا۟ بِٱلْحَقِّ وَتَوَاصَوْا۟ بِٱلصَّبْرِ
እነዚያ ያመኑትና መልካሞችን የሠሩት፣ በእውነትም አደራ የተባባሉት፣ በመታገስም አደራ የተባባሉት ብቻ ሲቀሩ፡፡
Surah 104: Al-Humazah — الهمزة
وَيْلٌۭ لِّكُلِّ هُمَزَةٍۢ لُّمَزَةٍ
ለሃሜተኛ ለዘላፊ ሁሉ ወዮለት፡፡
ٱلَّذِى جَمَعَ مَالًۭا وَعَدَّدَهُۥ
ለዚያ ገንዘብን የሰበሰበና የቆጣጠረው (ያደለበውም) ለኾነ ፤(ወዮለት)፡፡
يَحْسَبُ أَنَّ مَالَهُۥٓ أَخْلَدَهُۥ
ገንዘቡ የሚያዘወትረው መኾኑን ያስባል፡፡
كَلَّا ۖ لَيُنۢبَذَنَّ فِى ٱلْحُطَمَةِ
ይከልከል፤ በሰባሪይቱ (እሳት) ውስጥ በእርግጥ ይጣላል፡፡
وَمَآ أَدْرَىٰكَ مَا ٱلْحُطَمَةُ
ሰባሪይቱም ምን እንደ ኾነች ምን አሳወቀህ?
نَارُ ٱللَّهِ ٱلْمُوقَدَةُ
የተነደደችው የአላህ እሳት ናት፡፡
ٱلَّتِى تَطَّلِعُ عَلَى ٱلْأَفْـِٔدَةِ
ያቺ በልቦች ላይ የምትዘልቅ የኾነችው፡፡
إِنَّهَا عَلَيْهِم مُّؤْصَدَةٌۭ
እርሷ በእርግጥ በእነርሱ ላይ የተዘጋጀች ናት፡፡
فِى عَمَدٍۢ مُّمَدَّدَةٍۭ
በተዘረጋች አዕማድ ውስጥ (የተዘጋች ናት)፡፡
Surah 105: Al-Fil — الفيل
أَلَمْ تَرَ كَيْفَ فَعَلَ رَبُّكَ بِأَصْحَٰبِ ٱلْفِيلِ
በዝሆኑ ባለቤቶች ጌታህ እንዴት እንደሠራ አላወቅህምን?
أَلَمْ يَجْعَلْ كَيْدَهُمْ فِى تَضْلِيلٍۢ
ተንኮላቸውን በጥፋት ውስጥ (ከንቱ) አላደረገምን? (አድርጓል)፡፡
وَأَرْسَلَ عَلَيْهِمْ طَيْرًا أَبَابِيلَ
በእነርሱም ላይ መንጎች የኾኑን ዎፎች ላከ፡፡
تَرْمِيهِم بِحِجَارَةٍۢ مِّن سِجِّيلٍۢ
ከተጠበሰ ጭቃ በኾነ ድንጋይ የምትወረውርባቸው የኾነችን፤ (አዕዋፍ)፡፡
فَجَعَلَهُمْ كَعَصْفٍۢ مَّأْكُولٍۭ
ቅጠሉ እንደ ተበላ አዝመራም አደረጋቸው፡፡
Surah 106: Quraish — قريش
لِإِيلَٰفِ قُرَيْشٍ
ቁረይሽን ለማላመድ (ባለዝሆኖቹን አጠፋ)፡፡
إِۦلَٰفِهِمْ رِحْلَةَ ٱلشِّتَآءِ وَٱلصَّيْفِ
የብርድና የበጋን ወራት ጉዞ ሊያላምዳቸው ይህንን ሠራ፡፡
فَلْيَعْبُدُوا۟ رَبَّ هَٰذَا ٱلْبَيْتِ
ስለዚህ የዚህን ቤት (የከዕባን) ጌታ ይግገዙ፡፡
ٱلَّذِىٓ أَطْعَمَهُم مِّن جُوعٍۢ وَءَامَنَهُم مِّنْ خَوْفٍۭ
ያንን ከረኃብ ያበላቸውን ከፍርሃትም ያረካቸውን (ጌታ ያምልኩ)፡፡
Surah 107: Al-Ma'un — الماعون
أَرَءَيْتَ ٱلَّذِى يُكَذِّبُ بِٱلدِّينِ
ያንን በምርመራው የሚያስተባብለውን አየህን? (ዐወቅከውን?)
فَذَٰلِكَ ٱلَّذِى يَدُعُّ ٱلْيَتِيمَ
ይህም ያ የቲምን በኀይል የሚገፈትረው፤
وَلَا يَحُضُّ عَلَىٰ طَعَامِ ٱلْمِسْكِينِ
ድኻንም በማብላት ላይ የማያግባባው ሰው ነው፡፡
فَوَيْلٌۭ لِّلْمُصَلِّينَ
ወዮላቸው ለሰጋጆች፡፡
ٱلَّذِينَ هُمْ عَن صَلَاتِهِمْ سَاهُونَ
ለእነዚያ እነርሱ ከስግደታቸው ዘንጊዎች ለኾኑት፤ (ሰጋጆች)፡፡
ٱلَّذِينَ هُمْ يُرَآءُونَ
ለእነዚያ እነርሱ ይዩልኝ ባዮች ለኾኑት፡፡
وَيَمْنَعُونَ ٱلْمَاعُونَ
የዕቃ ትውስትንም (ሰዎችን) የሚከለክሉ ለኾኑት (ወዮላቸው)፡፡
Surah 108: Al-Kauthar — الكوثر
إِنَّآ أَعْطَيْنَٰكَ ٱلْكَوْثَرَ
እኛ በጣም ብዙ በጎ ነገሮችን ሰጠንህ፡፡
فَصَلِّ لِرَبِّكَ وَٱنْحَرْ
ስለዚህ ለጌታህ ስገድ፤ (በስሙ) ሰዋም፡፡
إِنَّ شَانِئَكَ هُوَ ٱلْأَبْتَرُ
ጠይህ (የሚጠላህ) እርሱ በእርግጥ (ዘሩ) የተቆረጠው ነው፡፡
Surah 109: Al-Kafirun — الكافرون
قُلْ يَٰٓأَيُّهَا ٱلْكَٰفِرُونَ
በላቸው «እናንተ ከሓዲዎች ሆይ!
لَآ أَعْبُدُ مَا تَعْبُدُونَ
«ያንን የምትግገዙትን (ጣዖት አሁን) አልግገዛም፡፡
وَلَآ أَنتُمْ عَٰبِدُونَ مَآ أَعْبُدُ
«እናንተም እኔ የምግገዛውን (አምላክም አሁን) ተገዢዎች አይደላችሁም፡፡
وَلَآ أَنَا۠ عَابِدٌۭ مَّا عَبَدتُّمْ
«እኔም ያንን የተገዛችሁትን (ወደፊት) ተገዢ አይደለሁም፡፡
وَلَآ أَنتُمْ عَٰبِدُونَ مَآ أَعْبُدُ
«እናንተም እኔ የምግገዛውን (ወደፊት) ተገዢዎች አይደላችሁም፡፡
لَكُمْ دِينُكُمْ وَلِىَ دِينِ
«ለእናንተ ሃይማኖታችሁ አልላችሁ፡፡ ለእኔም ሃይማኖቴ አለኝ፡፡
Surah 110: An-Nasr — النصر
إِذَا جَآءَ نَصْرُ ٱللَّهِ وَٱلْفَتْحُ
የአላህ እርዳታና (መካን) መክፈት በመጣ ጊዜ፤
وَرَأَيْتَ ٱلنَّاسَ يَدْخُلُونَ فِى دِينِ ٱللَّهِ أَفْوَاجًۭا
ሰዎችንም ጭፍሮች እየኾኑ፤ በአላህ ሃይማኖት ውስጥ ሲገቡ ባየህ ጊዜ፤
فَسَبِّحْ بِحَمْدِ رَبِّكَ وَٱسْتَغْفِرْهُ ۚ إِنَّهُۥ كَانَ تَوَّابًۢا
ጌታህን ከማመስገን ጋር አጥራው፡፡ ምሕረትንም ለምነው፡፡ እርሱ ጸጸትን በጣም ተቀባይ ነውና፡፡
Surah 111: Al-Masad — المسد
تَبَّتْ يَدَآ أَبِى لَهَبٍۢ وَتَبَّ
የአቡ ለሀብ ሁለት እጆች ከሰሩ (ጠፉ፤ እርሱ) ከሰረም፡፡
مَآ أَغْنَىٰ عَنْهُ مَالُهُۥ وَمَا كَسَبَ
ከእርሱ ገንዘቡና ያም ያፈራው ሁሉ ምንም አልጠቀመውም፡፡
سَيَصْلَىٰ نَارًۭا ذَاتَ لَهَبٍۢ
የመንቀልቀል ባለቤት የኾነችን እሳት በእርግጥ ይገባል፡፡
وَٱمْرَأَتُهُۥ حَمَّالَةَ ٱلْحَطَبِ
ሚስቱም (ትገባለች)፤ እንጨት ተሸካሚ ስትኾን፡፡
فِى جِيدِهَا حَبْلٌۭ مِّن مَّسَدٍۭ
በአንገትዋ ላይ ከጭረት የኾነ ገመድ ያለባት ስትኾን፡፡
Surah 112: Al-Ikhlas — الإخلاص
قُلْ هُوَ ٱللَّهُ أَحَدٌ
በል «እርሱ አላህ አንድ ነው፡፡
ٱللَّهُ ٱلصَّمَدُ
«አላህ (የሁሉ) መጠጊያ ነው፡፡
لَمْ يَلِدْ وَلَمْ يُولَدْ
«አልወለደም፤ አልተወለደምም፡፡
وَلَمْ يَكُن لَّهُۥ كُفُوًا أَحَدٌۢ
«ለእርሱም አንድም ብጤ የለውም፡፡»
Surah 113: Al-Falaq — الفلق
قُلْ أَعُوذُ بِرَبِّ ٱلْفَلَقِ
በል «በተፈልቃቂው ጎህ ጌታ እጠበቃለሁ፡፡
مِن شَرِّ مَا خَلَقَ
«ከፈጠረው ፍጡር ሁሉ ክፋት፡፡
وَمِن شَرِّ غَاسِقٍ إِذَا وَقَبَ
«ከሌሊትም ክፋት ባጨለመ ጊዜ፤
وَمِن شَرِّ ٱلنَّفَّٰثَٰتِ فِى ٱلْعُقَدِ
«በተቋጠሩ (ክሮች) ላይ ተፊዎች ከኾኑት (ደጋሚ) ሴቶችም ክፋት፡፡
وَمِن شَرِّ حَاسِدٍ إِذَا حَسَدَ
«ከምቀኛም ክፋት በተመቀኘ ጊዜ፤ (እጠበቃለሁ በል)፡፡»
Surah 114: An-Nas — الناس
قُلْ أَعُوذُ بِرَبِّ ٱلنَّاسِ
በል «በሰዎች ፈጣሪ እጠበቃለሁ፡፡
مَلِكِ ٱلنَّاسِ
«የሰዎች ሁሉ ንጉሥ በኾነው፡፡
إِلَٰهِ ٱلنَّاسِ
«የሰዎች አምላክ በኾነው፡፡
مِن شَرِّ ٱلْوَسْوَاسِ ٱلْخَنَّاسِ
«ብቅ እልም ባይ ከኾነው ጎትጓች (ሰይጣን) ክፋት፡፡
ٱلَّذِى يُوَسْوِسُ فِى صُدُورِ ٱلنَّاسِ
«ከዚያ በሰዎች ልቦች ውስጥ የሚጎተጉት ከኾነው፡፡
مِنَ ٱلْجِنَّةِ وَٱلنَّاسِ
«ከጋኔኖችም ከሰዎችም (ሰይጣናት እጠበቃለሁ በል)፡፡»